የተፋሰስ ልማት ሥራ ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ በተጓዳኝ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የጎላ ፋይዳ አለው – አቶ ማስረሻ በላቸው
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ የ2018 ዓ/ም የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ የተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በምዕራብ ኦሞ ዞን፣ መኒት ጎልዲያ ወረዳ እየተካሄደ ይገኛል። በመርሐግብሩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው፥ በክልሉ ከዚህ ቀደም በተከናወነው የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል። የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ ከተፈጥሮ ሀብት…
