Trendings

Getenesh Gebeyehu

የተፋሰስ ልማት ሥራ ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ በተጓዳኝ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የጎላ ፋይዳ አለው – አቶ ማስረሻ በላቸው

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ የ2018 ዓ/ም የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ የተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በምዕራብ ኦሞ ዞን፣ መኒት ጎልዲያ ወረዳ እየተካሄደ ይገኛል። በመርሐግብሩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው፥ በክልሉ ከዚህ ቀደም በተከናወነው የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል። የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ ከተፈጥሮ ሀብት…

Read More

ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ የ2018 ዓ/ም የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ የተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በተገኙበት በምዕራብ ኦሞ ዞን፣ መኤኒት ጎልዲያ ወረዳ እየተካሄደ ይገኛል። በክልሉ እየተከሰተ ያለዉን የመሬትና የተፈጥሮ ሀብት መመናመን እና የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል የመሬት ፣ የውሃና የሰው ሀብት መጠበቅ ፣ ማልማትና በላቀ ደረጃ በማቀናጀት ጥቅም…

Read More

“በሀገሩ ሉዓላዊነት የማይደራደር ሠራዊት ማፍራት ተጠናክሮ ይቀጥላል”- ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

ወቅቱን የሚመጥን ሠራዊት የማፍራት ተልዕኮ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አየር ኃይል ላስመረቃቸው እጩ መኮንኖች ማዕረግ የማልበስ ሥነ-ሥርዓት አከናውነዋል። በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግርም፣ “ኢትዮጵያ ቀደምት ሀገር በመሆኗ እና ካላት የጂኦ-ፓለቲካ አቀማመጥ አንጻር ጠላት ተደጋጋሚ ትንኮሳ ቢያደርግባትም ጀግኖች አርበኞች የተከበረች ሀገርን አስረክበውናል” ብለዋል። በዘመናዊ…

Read More

ሀገራዊ አጀንዳ ምን ዓይነት ቅርፅ ሊኖረው ይችላል?

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 መቋቋሙ የሚታወስ ነው፡፡ በዚሁ አዋጅ መግቢያ ላይ በሀገራችን ኢትዮጵያ በሚገኙ የተለያዩ የፓለቲካ እና የሀሳብ መሪዎች እንዲሁም የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል እጅግ መሰረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሀሳብ ልዩነቶች እና አለመግባባቶች መኖራቸው ተጠቅሶ ይህም ለኮሚሽኑ መመስረት እንደምክንያት ተቀምጧል፡፡ ‘’እጅግ መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች’’ ሊባሉ የሚችሉ ጉዳዮች የትኞቹ ናቸው? ይህንን ጉዳይ ለመረዳት…

Read More

“የላቀ የመከላከል አቅም ያለው የሰው ኃይል መገንባት ተችሏል” — ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ

የኢፌዴሪ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን ምክንያት በማድረግ፣ በጄትና በሄሊኮፕተር የበረራ ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ አብራሪዎችንና የቴክኒክ ባለሙያዎችን በድምቀት አስመርቋል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ፣ ተቋሙ ተለዋዋጭ የሆነውን የዘመኑን የጦርነት አውድ በሚገባ የተረዳና የላቀ የመከላከል ብቃት ያለው የሰው ኃይል መገንባት መቻሉን ገልጸዋል። በዕለቱ በጄት እና በሄሊኮፕተር በቂ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የ2018 በጀት ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቦንጋ ከተማ እያካኸደ ነው።

የምክክሩ መነሻ ነጥቦች ዙሪያ ማብራሪያ የሰጡት የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር ካሳ ውይይቱ በዋናነት ባለፉት 6 ወራት የተሰሩ ተግባራት አፈጻጸም ታይተው ለተቀሩት ተግባራት ጠቋሚ ነጥቦች ላይ ማብራሪያ እንደሚሰጥ ገልጸዋል። ኮሚሽነሩ አክለው እንደ ገለጹት ባለፉት ጊዜያት ከክልል እስከ ወረዳና ከተማ አስተዳደር ለተቋሙ የተሰጠውን ተልዕኮ መሠረት ያደረጉ የግምገማ አፈጻጸም እንዲገለጹ ይደረጋል ብለዋል። በወንጀል መከላከል ዘርፍ የመዝገቦች ምርመራ…

Read More

ከተማን ከቀበሌ የሚያገናኘው መንገድ በመገንባቱ በአካባቢያቸው ይታይ የነበረውን የመንገድ ችግር እንደፈታላቸው በዳውሮ ዞን ኢሳራ ወረዳ ሾታ ቀበሌ ነዋሪዎች ተናገሩ።

በኢሳራ ‎ወረዳ የመንገድ ትስስር የምግብ ዋስትና ፕሮግራም (RCFSP) ከ2017 ዓም መጨረሻ ጀመሮ ከባሌ – መነሳ 16ኪሜ የመንገድ ጥገና፣1 የስትራክቼር እና ባሌ _ሾታ 12.37ኪሜ አዲስ የመንገድ ግንባታ በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል። በዳውሮ ዞን ኢሳራ ወረዳ ሾታ ቀበሌ አንዳንድ ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት መንግስት የመንገድ ተደራሽነት ችግሮችን ለመቅረፍ በሰጠው ትኩረት ባሌ ከተማን ከሾታ ቀበሌ የሚያገናኘው…

Read More

ኢትዮጵያ ወረርሽኞችን የምትመክትበት አዲስ አቅም ገንብታለች፡- አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎcv c

መንግሥት የሀገሪቱን የጤና ሥርዓት በማዘመንና ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት ተግባራዊ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። ኢትዮጵያ ወረርሽኞችን የምትመክትበት አዲስ አቅም ገንብታለች ያሉት አፈ ጉባዔው፤ የጤና ሥርዓታችን ከመቼውም ጊዜ በላይ እየዘመነ ነው ብለዋል፡፡ አፈ ጉባዔው ይህንን ያሉት የማርበርግ ቫይረስ ወረርሽኝ ከኢትዮጵያ መጥፋቱን ተከትሎ ዛሬ በተዘጋጀው የማብሰሪያ መርሐ-ግብር ላይ ተገኝተው…

Read More

የማርበርግ ቫይረስ በዜጎች ላይ ሊያደርስ የነበረውን አስከፊ ጉዳት በጠንካራ የበሽታ መከላከል ሥርዓት መቆጣጠር ተችሏል

ማርበርግ ቫይረስ ሊያደርስ የነበረውን አስከፊ ጉዳት በተቀናጀና ጠንካራ የበሽታ መከላከል ሥርዓት መቆጣጠር መቻሉን የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለጹ። ኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስን ለመከላከል በወሰደችው የተቀናጀና አስቸኳይ ምላሽ አሰጣጥ ሥርዓት ቫይረሱን ማጥፋት ችላለች። በዚህም ኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና አደጋን በመከላከል በጥቅምት ወር ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስን ከወራት በኋላ ሙሉ በሙሉ ማጥፋት መቻሏን ተከትሎ የዕውቅናና ምስጋና መርሃ ግብር…

Read More

ኢትዮጵያ ለጀመረችው አረንጓዴ የኢኮኖሚ ሽግግር አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ወሳኝ ነው

ኢትዮጵያ ለጀመረችው አረንጓዴ የኢኮኖሚ ሽግግር አስተማማኝና ተመጣጣኝ የኃይል አቅርቦት ወሳኝ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ(ዶ/ር) ገለፁ። የቻይና ሳውዘርን ፓወር ግሪድ ቴክኖሎጂ እና የኤዳን ኤሌክትሮ ፓወር ግሩፕ ኢትዮጵያን የምስራቅ አፍሪካ የአረንጓዴ ቴክኖሎጂ ማዕከል የማድረግ ዓላማን የሰነቀ ስትራቴጂካዊ አጋርነት መስርተዋል። የአጋርነት ስምምነቱን የኤዳን ኤሌክትሮ ፓወር ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ እድሪስ አደም እና የቻይና ሳውዘርን ፓወር…

Read More