በባንካችን የደንበኞች የግል አካውንት ላይ የደረሰ ምንም አይነት ጉዳት የለም፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሰሞኑን አጋጥሞት የነበረውን የአገልግሎት መቋረጥ ችግር አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ በባንኩ የደንበኞች የግል አካውንት ላይ የደረሰ ምንም አይነት ጉዳት አለመኖሩን የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ይፋ አድርገዋል። ባንኩ የውስጥ አሰራሩን ለማዘመን ሲያደርግ በነበረው ሂደት አርብ መጋቢት 6 ሌሊቱን ጤናማ ያልሆነ የገንዘብ እንቅስቃሴ እንደነበረ የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ የተፈጠረው ክስተት ከሳይበር ጥቃት ጋር የተያያዘ አለመሆኑን አስታውቀዋል፡፡…
