ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት የሀገሪቱ ታላቁ የኒሻን ሽልማት ተበረከተላቸው
የኢፌዴሪ ጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንትና የጦር ሃይሎች ዋና አዛዥ ሳልቫ ኪር ማያርዲት የሀገሪቱ ታላቁ የኒሻን ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ ሽልማቱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለደቡብ ሱዳን ህዝብ ነፃነትና ሉአላዊነት መከበር ለከፈለው ታላቅ መስዋዕትነትና ላደረገው ድጋፍ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር በወቅቱ÷ ኢትዮጵያ በቸገረን ጊዜ ሁሉ መጠጊያችን እና መጠለያችን ከመሆኗም…
