በክልሉ 56 ሺህ ላሞችና ጊደሮችን በሰው ሰራሽ ዘዴና በተሻሻሉ ኮርማዎች ማዳቀል መቻሉ የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል 56 ሺህ 56 ሺህ ላሞችና ጊደሮችን በሰው ሰራሽ ዘዴና በተሻሻሉ ኮርማዎች ማዳቀል መቻሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገልጿል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በክልሉ በበጀት አመቱ 56 ሺህ ላሞችና ጊደሮችን በሰው ሰራሽ ዘዴና በተሻሻሉ ኮርማዎች በማዳቀል 26 ሺህ 610 ጥጆች ማግኘት መቻሉን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ገልጸዋል።…

Read More

የፓርቲውን፣ የመንግስት እና የአገራችን ስኬቶች ለአለም በማስተዋወቅ ውጤቶች ተመዝግበዋል።

ብልፅግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ከቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ጋር በመሆን የ2017 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ በአርባ ምንጭ ከተማ እያካሄደ ነው። በዚህ ወቅት የብልፅግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ ( ዶ/ር ) እንደተናገሩት የፓርቲውን፣ የመንግስት እና የአገራችን ስኬቶች ለአለም በማስተዋወቅ ውጤቶች ተመዝግበዋል። በኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋ እየተሻሻለ የመጣበት ነው ብለዋል።…

Read More

ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።

ኮሚሽኑ በክልሉ 34 ወረዳዎች የአደጋ ስጋት እንዳለባቸው አስታውቋል። የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዶክተር ለማ መሰለ በክልሉ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በመለየት በርካታ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውን አስታውሰዋል። በክልሉ 34 ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ 269 ቀበሌዎች የአደጋ ስጋት ቀጠናዎች ተብለው መለየታቸውን አንስተዋል። ከሰሞኑ በካፋ ዞን ጨና ወረዳ ኮዳ ቀበሌ በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ ከ290 በላይ ዜጎች ከመኖሪያቸው መፈናቀላቸውን ተናግረዋል። ከዝናብ…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአስተዳደር ብልጽግና ህብረት የ2017 ዓ/ም ዕቅድ አፈጻጸምና የ2018 ዓ/ም ዕቅድ ዙሪያ ከአባላት ጋር እየገመገመ ነው።

በበጀት ዓመቱ ታቅደው በብልጽግና ቤተሰብ ደረጃ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን የተመለከተ ሪፖርት ህብረቱ ሰብሳቢ አቶ ሳምሶን መለሰ አቅርበዋል ። የህብረቱ ሰብሳቢ ባቀረቡት ሪፖርት የብልጽግና ቤተሰብ በበጀት ዓመቱ ዕቅዳቸውን ውጤታማ እንዲያደርጉ ተገቢው የድጋፍና ክትትል ስራዎች መሰራታቸውን አብራርተዋል ። ከክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሚወርዱ ሀገር አቀፍና ክልል አቀፍ ይዘት ያሏቸውን ተልዕኮ ለመፈጸም እንዲያስችል የአባላት አቅም ግንባታ…

Read More

ለመሠረተ ልማት ጥያቄዎች መንግስት ምላሽ እየሰጠ በመሆኑ መደሰታቸውን የያዶታ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።

ለመልካም አስተዳደር ጥያቄዎቻችንን መንግስት ምላሽ እየሰጠ ያለበት ሁኔታ የሚያስደስት ነው ሲሉ የያዶታ ከተማ ነዋሪዎች ተናግረዋል። በካፋ ዞን ሳይለም ወረዳ መንግስት ለዘመናት የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆነው የሰነበቱ የልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ምላሽ እየሰጠ መምጣቱ ይበልጥ የህብረተሰቡን ተነሳሽነት እያሳደገ መምጣቱን ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል። ነዋሪዎቹ ከወረዳው አስተዳደር ጋር በመተባበር በራስ አቅም የተለያዩ የልማት ስራዎችን ማከናወን መቻላቸውን ተናግረዋል ።…

Read More

qበካፋ ዞን ሳይለም ወረዳ ከ78 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ግንባታቸው የተጠናቀቁ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተመረቁ ።we

የያዶታ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅና የያዶታ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ቀዶ ጥገና ማዕከል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ኮሌጁ በ 66 ነጥብ 9 ሚለዮን ብር አዲስ ባስገነባው ህንጻ የአስተዳደር ክፍል፣የተማሪዎች መማሪያ ክፍሎች እና ቤተመጻሕፍት ክፍል የተካተተበት መሆኑ ታውቋል። በሌላ በኩልም በክልሉ መንግስት ከ 11 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ የያዶታ…

Read More

ትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ መጀመር የትምርት ቤት ደረጃን ለማሻሻል ዕድል እንደፈጠረላቸው የቴፒ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ባለድርሻ አካላት ተናገሩ።

ህብረተሰቡን በማሳተፍም የትምህርት ቤቱን ደረጃ ለማሻሻል ትኩረት በመስጠት እየተሰራ እንደሆነም ተገልጿል ። የቴፒ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የወላጅ ተማሪ መምህር ህብረት ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ጀማል ኢሳ የትምህርት ቤቱን ደረጃ ለመቀየር ህብረተሰቡን በማስተባበር እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል ። በ1937 ዓ/ም እንደተመሠረተ የሚነገርለት ትምህርት ቤቱ የ80 ዓመት ቆይታውን ያህል እንዳልተለወጠ አቶ ጀማል ተናግረዋል ። ቁጭትን ወደ…

Read More

ሪፖርታዥ

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ፖሊሲ ሪፎርም የተቋማትን ዘላቂነት በማጽናት የመንግሥትን የማስፈጸም አቅም የሚያሳድግ ነው፡፡ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ፐብሊክ ሰርቪሲና ሰዉ ሀብት ልማት ቢሮ የተጀመረዉ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ፖሊሲ ሪፎርም ተፈጻሚነት ጅምር ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም የሪፎርም መርሀ-ግብር ነድፎ ችግሮቹን ደረጃ በደረጃ (በየምዕራፉ ከፋፍሎ) እየፈቱ ለመሄድ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም አስፈላጊነት እሙን መሆኑን የክልሉ ተብሊክ…

Read More

በክልሉ ባሉት ዞኖች የወባ በሽታ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ያለመ የፅዳት ዘመቻ እና የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው

‎ የወባ ወረርሽኙን በዘላቂነት ለመከላከልና ለመቆጣጠር እየተደረገ ባለው ከፍተኛ ጥረት አጠቃላይ የህብረተሰቡ የነቃ ተሳትፎ ሊያደርግ እንደሚገባምና ባለድርሻ አካላትም በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅ ተመልክቷል ። ‎ ክረምት መግባቱን ተከትሎ የወባ ስርጭት ከፍ እያለ በመሆኑ ህብረተሰቡን በማስተባበር የመከላከልና የመቆጣጠር ሥራ ለመስራት በየዞኖቹ የ90ቀን ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መገባቱንና ለዚህም ‎ማህበረሰቡ የአካባቢውን ንጽህና በሚገባ በመጠበቅ የወባ ወረርሽኝ ከሚያመጣው የጤና…

Read More

የፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር ሃና አረአያስላሴ ለመንግስታዊ ሥራ ጉዳይ ቦንጋ ከተማ ገቡ

የኢፌዲሪ ፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር ሃና አረአያስላሴ ለመንግስታዊ ሥራ ጉዳይ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግሥት ቦንጋ ከተማ ገብተዋል ። ሚኒስቴሯ ወደ ክልሉ ቦንጋ ከተማ ሲደርሱ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የክልል፣የካፋ ዞንና የቦንጋ ከተማ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል። ሚኒስትሯ ሃና አረአያስላሴ በክልሉ በሚኖራቸው ቆይታ በክልሉ እስካሁን ድረስ የተሰሩ የፍትህ ትራንስፎርሜሽን ሥራዎች…

Read More