በክልሉ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና በዘርፋ የስራ ዕድል ፈጠራን ለማጠናከር በእንሰሳት ሀብት ልማት ስራ ላይ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለፀ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ግብርና ቢሮ ለዞንና ወረዳ የእንስሳት ዘርፍ ሃላፊዎች እና ጤና ባለሙያዎች ክልላዊ የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን ማስጀመሪያ እና የእንስሳት ጤና ፓኬጅ ስልጠና መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። የክልሉ ግብርና ቢሮ የእንስሳት ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ እንሰሳት ጤና ዳይሬክቶሬት ከምግብ ሥርዓት ማጣናከሪያ ኘሮግራም ጋር በመተባበር በተዘጋጀው መድረክ ላይ በቢሮው የእንስሳት እና ዓሳ…

Read More

ዜና ሹመት!

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) የተለያዩ ሹመቶችን ሰጥተዋል። በብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት በተቀመጡ አቅጣጫዎች መሠረት ከክልል እስከ ታችኛው መዋቅር ያሉት አመራሮች የግምገማና የምዘና መድረክ በጥብቅ ዲስፕሊን በመምራት በክልል ደረጃ አመራሩን መልሶ የማደራጀት ሥራ ተከናዉኗል። የአመራር ስምሪቱ የአመራርን ውጤታማነት፣ ስነ ምግባርን እና ዝግጁነትን መሠረት በማድረግ በጥልቀት የተከናወኑ መሆኑን ተጠቁሟል። አዲስ የተሾሙና የተሸጋሸጉ አመራሮች መንግስትና ህዝብ የጣለባቸውን…

Read More

ምቹ የእናቶች ማቆያ በማዘጋጀትና ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት በመስጠት የእናቶችና ህፃናት ሞት መቅረፍ ይገባል፦ አቶ ኃይለ ዘውዴaxda

‎ ‎የክልሉ ጤና ቢሮ እናቶች፤ ህፃናት አፍላ ወጣቶች ጤና እና ስነ-ምግብ ዳይሬክቶሬት የ2017 ዓ.ም እና የ2018 ሩብ ዓመት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። ‎ ‎በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ጤና ቢሮ ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሀይሌ ዘውዴ ክልሉ ከተመሠረተ ወዲህ የጤና ተቋማትን ለማስፋፋት በሰጠው ትኩረት አዳዲስ ጤና ተቋማት ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። ‎ ‎በክልሉ…

Read More

ወጣቶች ሀገራቸውን ለመገንባት ከወትሮ በተሻለ ትጋት እንዲንቀሳቀሱ ጥሪ ቀረበ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ “የሴቶችና ወጣቶች አደረጃጀቶችን ያማከለ ንቅናቄ ለነገው ትውልድ ግንባታ ሚና አለው ” በሚል መሪ ሀሳብ ለባለ ድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየሰጠ ነው። በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ገነት መኩሪያ: ሀገራችን ለጀመረችበት የማንሰራራት ጉዞ የሴቶችና ወጣቶች ሚና ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። ወጣቶች ለሀገር ግንባታና…

Read More

ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን በመከላከል የፀጥታ ስጋት ተጋላጭነት መቀነስ እንደሚገባ ተገለጸ።

የኢፌዴሪ የሠላም ሚኒስቴር፤ “ሠላምን በማጽናት በልማት ማንሰራራት” በሚል መርህ ቃል ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሠላምና ፀጥታ መዋቅር የባለድርሻ አካላት ስልጠና በሚዛን አማን ከተማ እየሰጠ ይገኛል። በመድረኩ ክልላዊ የሠላም ሁኔታ አዝማሚያ ሰነድ በክልሉ የሠላምና ፀጥታ ቢሮ፣ ምክትል የቢሮ ሀላፊና የፀጥታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አለሙ ቀርበው ሰፊ ውይይት እየተደረገ ይገኛል። የመድረኩ ተሳታፊዎቹ በክልሉ የፀጥታ ስጋት…

Read More

ኢሬቻ:-ፍቅር፣ ሰላምና አንድነት የሚፀናበት ታላቅ እሴት ነው – አቶ ፍቅሬ አማን

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን፣ የኢሬቻ በዓል ፍቅር፣ ሰላም፣ አንድነትና ይቅር ባይነት የሚፀናበት ታላቅ ባህላዊ እሴት መሆኑን ገለጹ። አቶ ፍቅሬ ይህንን የገለጹት ለመላው የኦሮሞ ህዝብና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝቦች የእንኳን ለኢሬቻ በዓል አደረሳችሁ መልዕክታቸውን ባስተላለፉበት ወቅት ነው። በዓሉ የኦሮሞ ህዝብ የክረምቱን የጨለማ ወቅት አልፎ ወደ ብርሃን ዘመን በሰላም…

Read More

የገቢ አሰባሰብ ስረዓት በማሻሻል የክልሉን ገቢ ማሳደግ ተችሏል፦ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ገቢዎች ቢሮ፣በፍቃደኝነት ግብር የመክፈል ባህል እንዲዳብር ለማስቻል ያለመ የባለድርሻ አካላት ምክክር በሚዛን አማን ከተማ አካሂዷል። የክልሉ ገቢ የመሰብሰብ አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን የጠቆሙት የቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ፥ የገቢ አሰባሰብ ስርዓት በማሻሻል የገቢ አቅምን ትርጉም ባለው መልኩ ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል። በክልሉ የሚገኙ የሚዲያና ኮሚውኒኬሽን ተቋማት፣ የሃይማኖት ተቋማት እንዲሁም…

Read More

የሰቆጣ ቃል ክዳን ማስፋፊያ ፕሮግራም ውጤታማ እንዲሆን ቅንጅታዊ አሰራር ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ከክልሉ የምግብና ስርዓተ ምግብ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ጋር በመሆን ሲያካሄድ የነበረው የሰቆጣ ቃል ክዳን ፕሮግራም የ2017 ዓ.ም የአፈፃፀም ግምገማና የ2018 የጀት ዓ.ም የዕቅድ ዝግጅት መድረክ ተጠናቋል፡፡ በመድረኩ በፕሮግራሙ የተሰሩ ስራዎች አበረታች መሆኑ ከሪፓርቱ ለመመልከት የተቻለ ሲሆን በስርዓት-ምግብ ችግር የህፃናት መቀንጨርና የመቀጨጭ ለመቀነስ ፕሮግራሙ በታቀፉ ወረዳዎች ትኩረት ተሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው…

Read More

የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችና የህዝብ ግኑኝነት አመራሮች የገቢ አሰባሰቡ ውጤታማ እንዲኾን የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ገቢዎች ቢሮ፣በፍቃደኝነት ግብር የመክፈል ባህል እንዲዳብር ለማስቻል ያለመ የባለድርሻ አካላት ምክክር በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። የውስጥ ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ የክልሉ ህዝቦች ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ የአስተምህሮ ስራ ወሳኝ መኾኑን ነው የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ በመክፈቻ ንግግራቸው የገለጹት። የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችና የሚዲያ አመራሮች በክልሉ የገቢ አሰባሰብ ሥራው ውጤታማ…

Read More

በክልሉ ለኦዲት ግኝቶች ምላሽ በማይሰጡ ተቋማት ላይ የተጠያቂነትና ህግ የማስከበር ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል፦ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የኦዲት ግኝት አስመላሽ ግብረ-ሀይል በኦዲት ግኝት እርምት አወሳሰድ ላይ የአፈፃፀም ግምገማ መድረክ በቦንጋ ከተማ አካሂዷል፡፡ በመድረኩ በክልሉ በቤንች ሸኮና በካፋ ዞን በንግድና ኢንቨስትመንት እና በስራ ክህሎትና ኢንተርፕራይዝ መምሪያ የተደረገውን የክዋኔ እና አካባቢ ኦዲት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጓል፡፡ የክልሉ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር አቶ አስራት አበበ ባቀረቡት የሥራ ዕድል…

Read More