Trendings

አቶ ጸጋዬ ማሞ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አማካሪ ዴኤታ ሆነው ተሾሙ፡፡

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወይዘሮ ሸዊት ሻንካ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አማካሪ ዴኤታ ሆነው ለተሾሙት ለአቶ ፀጋዬ ማሞ አቀባበል አድርገዋል፡፡ ክቡር አቶ ፀጋዬ ማሞ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ በመሆን ሲያገለግሉ ቆይተዋል። የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ስኬታማ የስራ ዘመን እንዲሆንላቸው በማህበራዊ ትስስር ገጹ ተመኝቷል፡፡

Read More

325 ሺህ ሊትር ነዳጅ በቁጥጥር ስር ውሏል – ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)

በህገ-ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ 325 ሺህ ሊትር ነዳጅ በቁጥጥር ስር መዋሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ “በጥራት ወደ ተሳለጠ የንግድ ስርዓት” በሚል መሪ ሀሳብ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት የስድስት ወራት አፈጻጸም ግምገማ እየተካሄደ ነው፡፡ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳሉት፥ ባለፉት ስድስት ወራት በወጪ ንግድ ዘርፍ ወደ 3…

Read More

አቶ አደም ፋራህ በአዳማ ከተማ አስተዳደር የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትን ጎበኙ

በምክትል ጠቅላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ በአዳማ ከተማ አስተዳደር የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትን ጎበኙ። አቶ አደም ፋራህ፣ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በአዳማ ከተማ አስተዳደር በሁሉም የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በተናበበና በተቀናጀ መልኩ በአንድ ማዕከል ለመስጠት የተቋቋመውና “ጋዲሳ ኦዳ” የሚል ስያሜ የተሰጠውን…

Read More

በሕገ-ወጥ ድርጊት በሚሳተፉ አካላት ላይ የሚወሰደው ርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል፦አገልግሎቱ

በሕገ-ወጥ ድርጊት በሚሳተፉ አካላት ላይ የሚወሰደው ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ፡፡ አገልግሎቱ በሰጠው መግለጫ÷ የፋይናንስ ወንጀሎች በሀገር ላይ የሚያደርሱት ጉዳት ዘርፈ ብዙ እና ከፍተኛ መሆኑን አስረድቷል፡፡ በመሆኑ ኢትዮጵያ ወንጀሎቹን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተለያዩ ህጎችን አውጥታ በመተግባር እንደምትገኝም አስገንዝቧል፡፡ ለአብነትም በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ የማቅረብና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው…

Read More

በጎንደር የተመዘገቡ ስኬቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ሰላምን ማጽናት ይገባል – ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ

በጎንደር የተመዘገቡ ስኬቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ሰላምን ማጽናት እንደሚገባ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ገለጹ። ጥምቀት በጎንደር ፋሲለደስ ባህረ ጥምቀት የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የውጭ ሀገር ጎብኚዎች እና በርካታ ምዕመናን በታደሙበት በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት የጎንደር ከተማ የሚመጥናት የእድገት ማማ ላይ መውጣት የምትችልበት ዘመን ነው። የጎንደር ከተማ በፈጣን…

Read More

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

ጥምቀት ኢትዮጵያ ለዓለም ያበረከተችው የአደባባይ የወል በዓል ነው። በዓሉ ከሃይማኖታዊ በዓልነት ባሻገር የሚታይ ለዓለም በማይዳሰስ ቅርስነት የተበረከተ ሀብታችን ነው፡፡ የበዓሉ መሠረት ሃይማኖታዊ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ሃይማኖታዊ መሠረቱን እንደያዘ ባህላዊ እሴት እንዲኖረዉ ጭምር አድርገውታል፡፡ በዓሉ በየዓመቱ ሲከበር ከክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ባሻገር መላው ሕዝብ የሚታደምበት የዐደባባይ የወል በዓል ተደርጓል፡፡ ኢትዮጵያ ለዓለም ሕዝብ ያበረከተችው የማይዳሰስ ቅርስ ኾኖ መመዝገቡም…

Read More

ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ ለከተራና ጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በደማቅ ሁኔታ ለሚከበረው የከተራና ጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ሙሉ መልዕክታቸው እንደሚከተለው ቀርቧል፦ እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ! ጥምቀት፣ ከሰማየ ሰማያት ወረደ፣ በባሕር መካከልም ቆመ ብለን የምናከብረው በዓል ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ የሕዝቡን ችግር ለመፍታት ማድረግ ያለብንን አራት ነገሮች አስተምሮናል። እነዚህም ወደ ሕዝቡ መውረድ፣ ራስን አሳልፎ…

Read More

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት

እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ጥምቀት ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እና ኅብረ ብሔራዊ በዓላችን ነው። በሃይማኖታዊነቱ የኢየሱስ ክርስቶስን ከሰማያት ወርዶ፣ በዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ወንዝ መጠመቅ እናስብበታለን። ይሄም የጠፋውን አዳም ለመፈለግ የተደረገ ጉዞ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ አዳም በወደቀበት በእያንዳንዱ ዱካ ከቤተልሔም እስከ ቀራንዮ ተከትሎ ዋጅቶታል። በዚህም አዳምን ወደ ጥንት ክብሩ መመለስ ብቻ ሳይሆን ከጥንቱ የበለጠ ክብር ሰጥቶታል። ይሄም…

Read More

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል በአረንጓዴ የልማት ጉዞ በርካታ ተግባራትን በቁርጠኝነት በማከናወን ላይ ትገኛለች-ሳሙኤል ዶ (ዶ/ር)

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል በአረንጓዴ የልማት ጉዞ በርካታ ተግባራትን በቁርጠኝነት በማከናወን ላይ እንደምትገኝ የተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት የኢትዮጵያ ተወካይ ሳሙኤል ዶ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡ ሳሙኤል ዶ (ዶ/ር) እንዳሉት ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት አመታት በአረንጓዴ ልማት ያስመዘገበችው ውጤት አስደናቂ እና ለሌሎች ምሳሌ ሊሆን የሚችል ነው፡፡ “ኢትዮጵያ አረንጓዴ ጉዞ 2030” በሚል መሪ ሃሳብ አመታዊ የልማት ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ…

Read More

ለእናቶች የሚሰጡ የወሊድ አገልግሎቶችን ይበልጥ ለማዘመን እየተሰራ ነው – ዶክተር መቅደስ ዳባ

በጤና ተቋማት ለእናቶች የሚሰጡ አገልግሎቶችን በማዘመን በወሊድ ምክንያት የሚሞቱ ዜጎችን ህይወት ለመታደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለጹ። የጤናማ እናትነት ወር ”ጥራቱን የጠበቀ የምጥ እና የወሊድ እንክብካቤ ለሁሉም እናት፤ ለጤናማ እናቶች” በሚል መሪ ሀሳብ መከበር ጀምሯል። የጤናማ እናትነት ወር በአለም አቀፍ ደረጃ ለ38ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ19ኛ ጊዜ እየተከበረ ነው። የጤና ሚኒስትሯ…

Read More