Trendings

ብልፅግና ፓርቲ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ተጨባጭ ውጤት አስመዝግቧል – ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)

ብልፅግና ፓርቲ በመጀመሪያ ጉባኤው በገባው ቃል መሰረት የሴቶች ህፃናትና ወጣቶችን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ሚኒስትሯ ፓርቲው በመጀመሪያው ጉባኤ በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች የፈጸማቸውን ተግባራት በተመለከተ ለኢዜአ በሰጡት ማብራሪያ እንደገለጹት ራዕያችን በ2022 የዜጎች መብትና ጥቅም የተከበረባት፤ ማህበራዊ ጥበቃ የተስፋፋበት የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ…

Read More

“የኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ጥምረት ለጥራት ፕሮግራም የሆስፒታሎችን አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል ጠቃሚ ነው ” ዶክተር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስትር

የጤና ሚኒስቴር ያዘጋጀው አገር አቀፍ የኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ጥምረት ለጥራት ፕሮግራም የስድስት ወራት አፈጻጸም የግምገማ መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል። የግምገማ መድረኩ ማጠናቀቂያ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እንደተናገሩት እንደ ሀገር ጠንካራ የጤና ሥርዓት በመገንባት የአገልግሎት ጥራትን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ብለው የማህበረሰቡን የጤና አገልግሎት ፍላጎት ለማሻሻልና የሆስፒታሎችን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ጥምረት ለጥራት ፕሮግራም ጉልህ…

Read More

የምዕራብና የደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከመደበኛ በላይ ዝናብ ይኖራቸዋል

ኢንስቲትዩት የወቅት ትንበያ ይፋ ለማድረግ ባዘጋጀው የባለድርሻ አካለት መድረክ የባለፈውን የበጋ ወቅት ትንበያ የገመገመ ሲሆን በጋው በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ መደበኛ እና ከመደበኛ በላይ ዝናብ እንደተስተዋለባቸውና ይህም ሁኔታ በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው ለሆኑት በደቡብና ደቡብ ምስራቅ ለሚገኙ አርሶ እና አርብቶ አደሮች ምቹ ሁኔታን የፈጠረ እንደነበረ ተገልጿል፡፡ በእለቱ የመጪው በልግ ትንበያ ይፋ የተደረገ ሲሆን በልግ ዋነኛ…

Read More

የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት የጅማ ከተማን የተደበቀ ውበት ይበልጥ እንዲፈካ አድርጓል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጅማ የነበራቸውን ቆይታ አስመልከተው በሰጡት ማብራሪ ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት የታደለች ሀገር መሆኗን አውስተው÷ ቢሰራባቸው ዓለምን የሚያስደንቁ የተፈጥሮ ጸጋዎች በሁሉም የኢትዮጵያ ጫፍ እንዳሉ ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ መደመር የሚለው ሃሳብ ሲጀመር ሶስት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ እንደነበር የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ÷ የመጀመሪያው የኢትዮጵያን ተፈጥሮ፣ ጸጋና ሃብት በውል ማወቅ መቻል ነው ብለዋል፡፡ አሁን ላይ የጅማን…

Read More

መንግስት የባህል ዘርፉ እንዲጠበቅና እንዲጠናከር በትኩረት እየሰራ ይገኛል – የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ

መንግስት የባህል ዘርፉ እንዲጠበቅና እንዲጠናከር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ገለጹ። በኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የተዘጋጀ የ72ኛው የቦረና ገዳ ሥርዓት የባሊ ርክክብን በተመለከተ የፓናል ውይይት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። በመድረኩም የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፣ የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ጀሚላ ሲምቢሩ፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አብዱላዚዝ ዳውድ፣…

Read More

ለኢንዱስትሪዎች 369 ነጥብ 1 ሚሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ቀረበ

በግማሽ ዓመቱ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች 369 ሚሊየን 110 ሺህ ዶላር የውጭ ምንዛሪ መቅረቡን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 16ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ሲሆን÷በዚህም የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል የሚኒስቴሩን የ2017 ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን አቅርበዋል፡፡ በሪፖርታቸውም÷በግማሽ ዓመቱ ለተለያዩ አምራች ኢንዱስትሪዎች 9 ነጥብ 5 ሚሊየን ቶን በላይ ግብዓት ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል፡፡ አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ…

Read More

የተባበሩት መንግሥታት ሰብዓዊ መብትን በማስቀደም ሽብርተኝነትን መዋጋት እንደሚገባ አሳሰበ

ለሰብዓዊ መብትና ለሕግ የበላይነት ቅድሚያ በመስጠት ሽብርተኝነትን የሚያባብሱ መሰረታዊ ሁኔታዎችን እልባት መስጠት እንደሚገባም የተባበሩት መንግሥታት ምክትል ዋና ፀሐፊ አሚና መሃመድ አሳሰቡ። ምክትል ዋና ፀሐፊዋ በፀጥታው ምክር ቤት ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር፥ በአሁኑ ወቅት ሽብርተኝነት በሁሉም መልኩ በአፍሪካ ሰላም፣ ደኅንነት እና ዘላቂ ልማት ላይ ትልቁን አደጋ እያስከተለ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል። በተለይም ከሽብርተኝነት ጋር በተያያዘ በዓለም ከሚሞቱ…

Read More

በጅማ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የዐይን ባንክ ለመክፈት ዝግጅት ተጠናቀቀ

በቅርቡ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የዐይን ባንክ ለመክፈት የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ደም እና ኅብረ-ኅዋስ ባንክ አገልግሎት አስታወቀ፡፡ የዐይን ባንክ ተደራሽነትን ለማስፋፋት ጥረት እየተደረገ መሆኑን የገለጹት የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሀብታሙ ታዬ÷ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል በቅርቡ የሚከፈተው የዐይን ባንክ የዚሁ ሥራ አካል ነው ብለዋል፡፡ ባንኩን ለመክፈትም የቦታ ዝግጅት እና የግብዓት አቅርቦት መጠናቀቁን ጠቅሰው÷ በቅርቡ የሰው…

Read More

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ውይይት እየተካሄደ ነው

በመድረኩ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪውን መዋቅራዊ ችግሮች በቅንጅት ከመፍታት እና ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን እንዲወጡ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ውጤት እያመጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የንቅናቄውን አፈፃፀም ለመገምገም እና ለመደገፍ የሚኒስትሮች የክትትል እና የድጋፍ ቡድን በክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች በቅርቡ የመስክ ምልከታ በማድረግ ድጋፍ ማድረጉም ተመላክቷል፡፡ ቡድኑ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አፈፃፀምን በተመለከተ ባመጣው ግኝት ላይና አፈፃፀሙ በየክልሎች ያለበትን…

Read More

የሰቆጣ ቃልኪዳን ትግበራን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ የፕሮግራሙን ተደራሽነት ማስፋት ይገባል – የምግብ ስርዓትና ኒውትሪሽን ስትሪንግ ኮሚቴ

የሰቆጣ ቃልኪዳን ውጤታማነት ለማሳደግ ተደራሽነቱን ለማስፋት በትኩረት መስራት እንደሚገባ የምግብ ስርዓትና ኒውትሪሽን ጥምር የሚኒስትሮች ስትሪንግ ኮሚቴ አስታወቀ። የጤና ሚኒስቴር እና የግብርና ሚኒስቴር በጋራ የሚያስተባብሩት የሚኒስትሮች ስትሪንግ ኮሚቴ ስብሰባ ተካሂዷል። ውይይቱ በኮሚቴው ስር የሚገኙ 15 ሴክተር መስሪያ ቤቶችን ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር አላማ ያደረገ ነው። በሰቆጣ ቃልኪዳን ፕሮግራም፣ በኢትዮጵያ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽንና ኒውትሪሽን ሴክሬተሪያት የተሰሩ ስራዎችና የተገኙ…

Read More