Trendings

የሌማት ትሩፋት ለግብርና ኢንቨስትመንትና ለሀገራዊ የስርዓተ ምግብ መሻሻል ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑ ተገለፀ

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በደብረ ብርሃን ከተማ በሌማት ትሩፋት የተሰማራ የውጭ ባለሃብት የሥራ እንቅስቃሴን ተመልክተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ባቀድነው መሠረት በውጤታማነት እየተተገበረ ነው ብለዋል። የተመጣጠነ የምግብ ዋስትና ስርዓትን ለማረጋገጥ በሁሉም መስክ የተጀመሩ ሥራዎች የሚበረታቱ ናቸው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የደብረ-ሆላንድ የዶሮና እንቁላል ምርት ማዕከልም ሀገራዊ ውጥንን ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ማዕከሉ…

Read More

በክልሉ ዓለምአቀፍ የህጻናት ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች ተከበረ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ 35ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ19ኛ ጊዜ “ህፃናት የሚሉት አላቸው እናዳምጣቸዉ !” በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የህፃናት ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች በቦንጋ ከተማ ተከብሯል። የህጻናት መብትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ተጠናከሮ መቀጠል እንዳለበት የገለጹት የክልሉ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ…

Read More

በዘንድሮው በጀት አመት ከ1ሺህ 7ሄክታር በላይ መሬት በበጋው መስኖ ስንዴ ለማልማት መታቀዱ ተገለፀ።

በምዕራብ ኦሞ ዞን የ2016 የበጋው መስኖ ስንዴ እቅድ አፈጻጸም እና የ2017 እቅድ እንዲሁም በልማት ትሩፋት ሥራዎች ዙሪያ ዉይይት እየተደረገ ይገኛል። በመድረክ የዞኑ ዋና አስተዳደሪ አቶ ጌታቸዉ ኬኒ እንደተናገሩት የበጋ መስኖ ስንዴ የልማት ሥራዎች ከአምናው በነበረው ልምዶች በዘንድሮው የተሻለ ምርት ለማግኘት መትጋት ይጠበቃል ብልዋል። አያይዘውም በ2016ዓም 488ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ መሸፈኑ የገለፁት ዋና አስተዳደሪ ይህ…

Read More

የቱሪዝም ሀብቶች መጠበቅ፣ለትውልድ መተላለፍ እና መጠቀም መቻል እንደለበት የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው ነጋሽ ገለጹ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት የባህል ፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ብላቴ የተመራ የፌዴራል፣ የክልልና የተለያዩ ሚዲያ አካላት ልዑካን በካፋ ዞን ጉርጉቶ የእግዜር ድልድይ የቦንጋ ብሔራዊ የቡና ሙዝዬም ጎብኝተዋል። ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው ነጋሽ በጉብኝቱ በዩትና በሰሙት በጣም ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው በዚህ ቦታ የተገኝንበት ዋና አላማ የዓለም የቱሪዝም ቀንን ምክንያቱ…

Read More

የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ስርጭት መከላከልና መቆጣጠር ላይ የባለድርሻ ተቋማት ሚና እንዲጠናከር ተጠየቀ

በክልሉ የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ስርጭትን መከላከልና መቆጣጠር ላይ የባለድርሻ ተቋማትና አካላት ሚና እንዲጠናከር የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ጠይቋል። የክልሉ ጤና ቢሮ ለሴክተር መስሪያ ቤቶችና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኤች .አይ.ቪ ሜይንስትሪሚንግ ስልጠና በቦንጋ ከተማ እየሰጠ ይገኛል። የክልሉ ጤና ቢሮ ኤች.አይ.ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መንግስቱ ካሰሪ በክልሉ 14 ሺህ የቫይረስ ተጠቂ ይገኛል…

Read More

ሰው ተኮር ተግባር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መገለጫ ነው፦አቶ አለማየሁ አለሙ

የሸካ ዞን ሴቶች ህፃናት ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የ2016 ዓ.ም የክረምት ወራት ወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት መዝጊያ ፕሮግራም በማሻ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት በብልፅግና ፓርቲ ሸካ ዞን ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ አለሙ ሰው ተኮር ተግባር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መገለጫ መሆኑን ጠቁመው ሁሉም በትኩረት ልተገብረው ይገባል ሲሉም ገልፀዋል። የበጎ…

Read More

ዓለም አቀፍ የህፃናት ቀን “ህፃናት የሚሉት አላቸው እናዳምጣቸው! ” በሚል መሪ ቃል እንደሚከበር ተገለጸ

የዘንድሮ ዓለም አቀፍ የህፃናት ቀን ለማክበር ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገልጿል ፡፡ የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ገነት መኩሪያ እንደገለጹት ዓለም አቀፍ የህፃናት ቀን የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌ አካል የሆነው የአለም ህጻናት መብቶች ኮንቬንሽን እ.ኤ.አ ኑቬምበር 20/1989 ዓ.ም በተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባዔ ፀድቆ በስራ ላይ እንዲውል…

Read More

የዘንድሮው የአለም የቱሪዝም ቀን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለ3ኛ ጊዜ“ቱሪዝም ለሠላም ” በሚል መሪ ቃል በቦንጋ ከተማ መካሄድ ጀመረ

የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዮት ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ ባህል፣ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር በዓለም 45ኛ ጊዜ በሀገራችን ለ37ኛ ጊዜ እና በክልላችን ለ3ኛ ጊዜ የሚከበርው የቱሪዝም ቀን ‹‹ቱሪዝም ለሰላም›› በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የቱሪዝም አለኝታ ጥናታዊ ጽሁፍ የውይይትና የንቅናቄ መድረክ የሚሳተፉበት ከፌዴራል እና ከክልሉ ሁሉም ዞኖች የመጡ የመድረኩ ተሳታፊዎች በካፋ ባህል አዳራሽ ተገኝተዋል። በመድረኩ የክልሉ…

Read More

አደረጃጀቶች የሕዝብን የሰላምና የልማት ጥያቄ ለመመለስ ፋናወጊ ሆነው ሊንቀሳቀሱ ይገባል፦የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ክቡር አቶ ፍቃዱ ተሰማ

የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት “የጠንካራ አደረጃጀት ትጋት ለአገራዊ ህልሞቻችን ስኬት” በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የነበረውን የ2017 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ አጠናቋል፡፡ በመድረኩ ማጠቃለያና የስራ መመሪያ የሰጡት በሚኒስትር ማዕረግ የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ክቡር አቶ ፍቃዱ ተሰማ አደረጃጀቶች ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የህዝብ ጥያቄ ለመመለስ እንዲሁም ልማትን በማረጋገጥ ሚናቸውን በመለየት እስከታችኛው የህብረተሰብ…

Read More

በክልሉ ያሉ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆችን ተልዕኮን ለማስፈጸም በሚችል መልኩ ማጠናከር ይገባል፦ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ስራና ክህሎት ቢሮ ክልላዊ የክህሎት መር የስራ ዕድል ፈጠራ የንቅናቄ መድረክ ተጠናቋል። በክህሎት መር የንቅናቄ መድረክ የተሳተፉ ባለድርሻ አካላት በነበረው ውይይት ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ አስተያየቶችን ሰጥተዋል። ተሳታፊዎች ባነሱት አስተያየት በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ብቁና ጥራት ያለው ሰልጣኝን ከማፍራት አንጻር ክፍተቶች መኖራቸውንና ይህንንም ችግር ለመቅረፍ ትኩረት አድርገው እንደሚሰሩ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።…

Read More