Trendings

በክልሉ ያለውን እምቅ የግብርና አቅም በተሻለ መልኩ ለመጠቀም የባለድርሻ አካላት ድጋፍ መጠናከር እንዳለበት ተጠየቀ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ በክልሉ ያለውን እምቅ የግብርና አቅም በተሻለ መልኩ ለመጠቀም የሚስችል የመካከለኛ ዘመን ስትራቴጂካዊ እቅድ ዝግጅት ላይ ለባለድርሻ አካላት በሚዛን አማን ከተማ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታመነ በቀለ በስልጠናው መግቢያ ባደረጉት ንግግር በክልሉ ያለውን እምቅ የግብርና አቅም በተሻለ መልኩ ለመጠቀም…

Read More

በክልሉ የግብርና ልማት ስራዎችን የሚደግፍ (PACT) ፕሮግራም ለባለድርሻ አካላት ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ተሳትፏዊ ግብርና ለአየር ንብረት ሽግግር በእንግሊዝኛ ምህጻረ ቃል PACT ፕሮግራም ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በሚዛን ከተማ እየሰጠ ይገኛል። ፕሮግራሙ በመጀመሪያው ምዕራፍ በክልሉ በአነስተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረጉን የገለጹት በክልሉ ግብርና ቢሮ የተሳትፏዊ ግብርና ለአየር ንብረት ሽግግር ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ታመነ ተስፋዬ አሁን ላይ ወደ…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የባለድርሻ አካላት አጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር መድረክ ተጀመረ

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለባለድርሻ አካላት ያዘጋጀው አጀንዳ የማሰባሰብ እና ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተወካዮች መረጣ መድረክ ተጀምሯል። ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘገየ አስፋው በመድረኩ ባስተላለፉት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት የፖለቲካ፣ የማህበራዊ እና የኢኮኖሚ ችግር እንዳለባት ጠቁመው ይህንን ችግር በምክክርና በውይይት ፈተን ወደ ፊት ማራመድ አለብን ሲሉ…

Read More

የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ የአባላቱን አቅም መገንባት ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ

የክልል ተቋማት የቴፒ ማዕከል ፐብሊክ ሰርቫንት የብልፅግና ፓርቲ አባላት በ4ኛ ዙር “የህልም ጉልበት፣ ለእመርታዊ ዕድገት!” በሚል መሪ ቃል ስሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል። በአባላት ስልጠና ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ መቱ አኩ እንደተናገሩት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ የአባላቱን አቅም መገንባት ወሳኝ ነው ብለዋል። እስካሁን የተመዘገበው በሁሉም ዘርፍ የፖለቲካዊ ፣…

Read More

አመራሩና አባሉ የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠልና የብልጽግና ህልሞችን መዳረሻ ለመድረስ በትጋት መስራት ያስፈልጋል ፦ ኢንጂነር በየነ በላቸው

በቦንጋ ማዕከል የመሠረታዊ ድርጅት አመራሮችና አባላት “የህልም ጉልበት ለእመርታዊ እድገት” በሚል መሪ ሀሳብ ሲሰጥ የነበረው የአቅም ግንባታ ስልጠና በስኬት ተጠናቋል ። ሰልጣኞቹ ብልፅግና ፓርቲ የተመሠረተበት 5ኛ ዓመት ክብረ በዓል በተለያዩ ሁነቴቶች አክብረዋል። የክልሉ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር በየነ በላቸው በማጠቃለያ መድረክ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት አመራሩና አባሉ በተሰማራበት መስክ ሁሉ አገልጋይ ተኮር እሳቤን…

Read More

የ4 ክልሎች የጋራ ሃብት የሆኑ የልማት ድርጅቶች አፈጻጸም ግምገማ እየተካሄደ ነው

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች፣ የደቡብ ኢትዮጵያ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና የሲዳማ ክልሎች የጋራ ሃብት የሆኑ የመንግስት የልማት ድርጅቶች አፈጻጸምና አጠቃላይ ተቋማቱ ያሉበትን ደረጃ የሚገመግም የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡ በቀድሞው የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል መንግስት ተቋቁመው የነበሩ እና አራቱም ክልሎች ሲደራጁ የጋራ ሃብት ሆነው እንዲቀጥሉ የተወሰኑ የመንግስት የልማት ድርጅቶች አፈጻጸም ነው እየተገመገመ የሚገኘው፡፡ የደቡብ…

Read More

ብልፅግና ፓርቲ የተመሠረተበት 5ኛ ዓመት ክብረ በዓል ተከበረ

የክልል ተቋማት የቦንጋ ማዕከል የአስተዳደር ዘርፍ መሠረታዊ ድርጅት አመራሮችና አባላት ብልፅግና ፓርቲ የተመሠረተበት 5ኛ ዓመት ክብረ በዓል አክብረዋል። በክብረ በዓል አከባበር ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፈ አቶ ነጋ አበራ ለመላው ለፓርቲው አባላት እና ደጋፊዎች እንኳን ለፓርቲያችን 5ኛ ዓመት ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን ። ፓርቲያችን ብልፅግና ፓርቲ…

Read More

የሀገራዊ ምክክሩ ኮሚሽን የአጀንዳ ቀረጻና የምክክር አስተባባሪ አቶ ተመስገን አብዲሳ አጀንዳና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል ።

አቶ ተመስገን አብዲሳ ለኮሚሽኑ በአጀንዳነት የሚቀርቡ አጀንዳዎች አጀንዳ የሚያስብላቸው መገለጫ ባህሪያቸው፣ የአጀንዳዎቹ መዳረሻቸው የት እንደሆነ፣ የአጀንዳ ባህሪያትስ ምንድናቸው? የኮሚሽኑ የአጀንዳነት መስፈርት ምን ምንድ ናቸው ? በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ለሚዲያ ማብራሪያ ሰጥተዋል ። አቶ ተመስገን በሰጡት ማብራሪያ በሀገር አቀፉ የምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ላይ በመግቢያው የተገለጸውን ጉዳይ መሠረት በማድረግ ልዩነቶች መኖራቸውንና ለምክክሩ ምክንያት መሆናቸውን አብራርተዋል።…

Read More

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚያከናዉናቸው ተግባራት ውጤታማ እንዲሆን የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ የድጋፍና ክትትል ስራዎችን እንደሚያጠናክር አስታወቀ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ፋይናንስ ቢሮ እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የ3ኛ ዙር የጋራ ምክክር መድረክ በሚዛን ከተማ አካሂዷል ። በምክክር መድረኩ በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅች በኩል የተከናወኑ የስራ አፈጻጸም ረፖርት ቀርበው ከተሳታፊዎች ሀሳቢና አስተያየት ተነስተው ውይይት ተደርጎበታል። በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ መቱ አኩ እንደተናገሩት ድርጅቶች በክልሉ በተለያዩ ዘርፎች…

Read More

የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደቱ ግለፀኝነትና አሳታፊ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮች ገለፁ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል እየተከናወነ ያለውን 3ኛ ቀኑን የያዘውን የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ አስመልክቶ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በቦንጋ ከተማ መግለጫ ሰጥቷል። በመግለጫው ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሉጌታ አጎ የእስካሁን ያለውን የምክክሩን ሂደት ከሁሉም ወረዳዎች የተመረጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ወኪሎች ግልጽና አሳታፊ በሆነ መልኩ አጀንዳቸውን አደራጅተው ያጠናቀቁበት የምክክር መድረክ መሆኑን ገልፀዋል። በክልሉ የህብረተሰብ ወኪሎች…

Read More