Trendings

ጉልበት ቆጣቢው የሩዝ ምርት – በሸካ ዞን

መንግሥት የአገር ውስጥ ገበያ ፍላጎትን በሀገር ውስጥ ምርት ለመሸፈን ትኩረት አድርጎ እየሰራበት ካለው የብርዕ ሰብሎች አንዱ ሩዝ ነው። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልም በዘንድሮው የምርት ወቅት 13 ሺህ 452 ሄክታር መሬት በሩዝ ዘር ተሸፍኗል። በሸካ ዞን ቆይታችንም በአርሶአደሩ ዘንድ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሩዝ እርሻ ተመራጭ እየሆነ መምጣቱን መመልከት ተችሏል። በዞኑ በዘንድሮው መኸር 2 ሺህ የሚጠጋ…

Read More

የሸካ ዞንን ሰላም በማጽናት በሁሉም ዘርፎች ዉጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ ተገለጸ

የሸካ ዞንን ሰላም በማጽናት በሁሉም ዘርፎች ፊት እንዲወጣና በቀጣይ 5 ዓመታት የተያዙ የልማት ዕቅዶች ዙሪያ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በቴፒ ከተማ ውይይት ተካሂዷል የከተማ ኮሪደር ልማቶች፣የመልሶ ማልማት ፣ከተማን ለኢንቨስትመንት ማዘጋጀትና መከታተል በማህበራዊና በኢኮኖሚ ዘርፍ በተለይ አዳሪ ትምህርት ቤት በመክፈት ተወዳዳሪ ትዉልድ ለመፍጠርና በሌሎችም የልማት ሥራዎች ዙሪያ ምክክር ተካሂዷል። በመድረኩ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮዽያ ህዝቦች ክልል በምክትል…

Read More

በታሪክ ተመራማሪው አቶ አሰፋ ገብረማርያም እና በአቶ አዕምሮ ገሰሰ የተጻፈ መጸሐፍ በቦንጋ ከተማ ተመረቀ፡

መጸሐፉ የካፈቾ ህዝብ ባህል እና ታሪክ ላይ ያተኮረ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ የመጸሐፉ ደራሲ አቶ አሰፋ ገብረማርያም መጽሐፉ ሰባት ምዕራፎችና 3 መቶ 36 ገጾች ያሉት እንዲሁም የካፈቾ ባህል እና ታሪክ ላይ ያተኮረ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የካፈቾ ብሔር ማንነትን፣ የጎንጋ ህዝቦች ትስስርን፣ ጥንታዊ የካፋ መንግስት አመሰራርንና ሌሎችንም ሀሳቦች ስለማካተቱ ገልጸዋል፡፡ መጽሐፉ ለታዳጊ ደራሲዎች መነሻ እንደሚሆን ገልጸው ፤ ለህትመት እንዲበቃ…

Read More

የክልሉን ሠላም በዘላቂነት ለማጽናት የሚያበረታቱ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ተናገሩ።

ይህ የተገለጸው የመልካም አስተዳደርና ህግ ጉዳዮች ዘርፍ ተቋማት የአፈጻጸም ሪፖርት በቀረበበት ነው። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የ2017 በጀት ዓመት የአንደኛው ሩብ ዓመት የአፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል። የአፈጻጸም ሪፖርቱን ያቀረቡት የርዕሰ መስተዳድሩ የመልካም አስተዳደርና ህግ ጉዳዮች አማካሪ የሆኑ አቶ አክሊሉ ከበደ የሚያስተባብሯቸውን ተቋማት የአፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል ። ባቀረቡት የአፈጻጸም ሪፖርት በየተቋማቱ የሚያበረታቱ…

Read More

በማጂ ቱም ከተማ አ/ር የማጂ ከተማ የሶላር መብራት አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት በመስጠት እየተሰራ ነው ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በማጂ ቱም ከተማ ለዘመናት የህዝብ ጥያቄ የሆነው ይኸው የኤሌክትሪክ አቅርቦት ጥያቄን ምላሽ ለመስጠት መንግስት ትኩረት በመስጠት እየሰራ ይገኛል ። ችግሮቹን ለመቅረፍ የሶላር ቁሳቁስ የያዙ አምስት የጭነት መኪናዎች ከአዲስ አበባ ተነስተው ማጂ ከተማ መድረሳቸውን የማጂ ቱም ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል።

Read More

#ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው!

#ደቡብ_ምዕራብ_ኢትዮጵያ እጅግ መሰረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚታየውን አመግባባት ለመፍታት አካታች እና አሳታፊ በሆነ መልኩ ምክክር ማድረግ ወሳኝ ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያም ይህንኑ አምናበት ሁሉም ዜጎች የሚሳተፉበት ምክክር በማድረግ ላይ ትገኛለች። እርስዎም ሀሳብዎ ለሀገራችን ችግሮች መፍትሄ እንደሚሆን አውቀው በምክክሩ በንቃት ይሳተፉ! ኮሚሽኑ በመጪው እሁድ ጥቅምት 24/2017 ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚጀምረው የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ የቅስቀሳና…

Read More

ትምህርት ቤቶች የውስጥ ገቢን ማሳደግ ለትምህርት ጥራት ያለው አስተዋጽኦ የላቀ ነዉ። አቶ አልማው ዘውዴ

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ትምህርት ቤቶች የውስጥ ገቢን ማሳደግ ለትምህርት ጥራት ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን ገልጸዋል ። በ2016 ዓ/ም በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳደር በጨታ ሙሉ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት በበልግ እርሻ 141 ነጥብ 5 ኩንታል የበቆሎ ሰብል ምርት መገኘት መቻሉን…

Read More

በካፋ ዞን አዲዮ ወረዳ በጣለዉ ከባድ ዝናብ በተከሰተ የመሬት ናዳ አራት የአንድ ቤተሰብ አባላት ህይወታቸዉ ማለፋን ፖሊስ አስታወቀ

በዞኑ አዲዮ ወረዳግራዋ ሽሽማ ቀበሌ በሌ ልማት ቡድን ተብሎ በሚጠራበት ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት በጣለዉ ከባድ ዝናብ ባስከተለዉ የመሬት መንሸራተት አራት የአንድ ቤተሰብ አባላት በመኖሪያ ቤት ዉስጥ እንዳሉ ህይወታቸዉ ማለፋን ፖሊስ ገልጿል። በአደጋዉ ሁለት መኖሪያ ቤቶች በናዳዉ መወሰዱን ያመለከተዉ ፖሊስ በአከባቢዉ የሚጥለዉ ከባድ ዝናብ የነፍስ አድኑን ስራ አስቸጋሪ አድርጎታል።

Read More

የዞኑን ልማት በማፋጠን የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሁሉም ተሳትፎና ርብርብ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ

ይህ የተባለው በሸካ ዞን ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ በትኩረት በሚፈፀሙ ተግባራት ላይ ያተኮረ ውይይት በቴፒ ከተማ እየተካሄደ በሚገኝበት ወቅት ነው። የውይይት መድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ በወቅቱ እንደተናገሩት የዞኑን ልማትና እድገት ለማፋጠን እንዲሁም የዞኑን ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፎና ርብርብ ወሳኝ ነው ብለዋል። አቶ…

Read More

በአንደኛው ሩብ ዓመት የተገኘውን ውጤት በማስቀጠል በ2ኛው ሩብ ዓመት የላቀ አፈጻጸም ማስመዝገብ ይገባል። ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር ኢ/ር)።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የ2017 በጀት ዓመት የአንደኛ ሩብ ዓመት አፈጻጸም እየተገመገመ ነው። የርዕሰ መስተዳድሩ የኢኮኖሚና መሠረተ ልማት ጉዳዮች አማካሪ ዶክተር ኢንጂነር ምትኩ በድሩ የኢኮኖሚ ዘርፍ ተቋማትን የአፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል ። ሪፖርቱን ያቀረቡት አማካሪው በነዚህ ተቋማት ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ ተጨባጭ እና ውጤታማ የሆኑ ተግባራት መከናወናቸውን በሪፖርቱ አመላክተዉ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን ለይተዉ ለዉይይት አቅርበዋል።…

Read More