በምርጫው ሂደት በነፃነትና ሰላማዊ በሆነ መልኩ ድምፃቸውን መስጠታቸውን መራጮች ገለጹ
በምርጫው ሂደት በነፃነትና ሰላማዊ በሆነ መልኩ ድምፃችንን መስጠት ችለናል ሲሉ የመስቃንና ማረቆ ሁለት ምርጫ ድምፃቸውን የሰጡ መራጮች ተናገሩ። የድጋሚና ቀሪ ምርጫ በሚካሄድባቸው አካባቢዎች ቁሳቁሶች ተሟልተው በተለያዩ አካባቢዎች በዛሬው እለት መራጮች ድምጽ ሰጥተዋል። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልም የመስቃንና ማረቆ ሁለት የምርጫ ክልል ነዋሪዎች ከማለዳው ጀምረው የድጋሚ ምርጫ አካሂደዋል። የምርጫ ሂደቱን አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው መራጮች ሂደቱ ፍፁም ሰላማዊና…
