በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መንግስት በካፋ ዞን ሺሽንዳ ከተማ አስተዳደር “የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች” በሚል መሪ ቃል ከከተማ ነዋሪዎች ጋር ውይይት እየተካሄደ ነው፡፡
ውይይቱ በዞኑ በሚገኙ ሁሉም የከተማ አስተዳደር መዋቅሮች በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት እየተከናወነ ይገኛል ። በውይይት መድረኩ ላይ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጽያ ህዝቦች ክልል መንግስት ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ወሰነች ቶማስ፣ የካፋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ደመላሽ ንጉሴን ጨምሮ የሺሺንዳ ከተማ ነዋሪዎች አመራሮች ተገኝተዋል። በመድረኩ ባለፉት የለውጥ አመታት በመንግስትና በህዝብ ትብብር የተገኙ ውጤቶችና የቀጣይ…
