Trendings

129ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ምክንያት በማድረግ በታርጫ ከተማ በአካላዊ እንቅስቃሴና ፅዳት ዘመቻ ተካሄደ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አክልሉ ለማ የዛሬው ትውልድ ዳግም አድዋን በመድገም በኢኮኖሚ አሸናፊነት እና ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ያጠናከረ ዜጋ በማፍራትና ከተሞች ለኑሮ ምቹ እንዲሆኑበ ማድረግ ዘወትር በየሣምንቱ የፅዳት ዘመቻ ማድረግንእንደምገባም አሳስበዋል ። የታርጫ ከተማ ከንቲባ አቶ ዳዊት ወንድሙ በበኩላቸው ከተሞች ለነዋሪዎች ምቹ እንዲሆኑ የተጀመረው የጽዳት ዘመቻ በየሣምንቱ…

Read More

የመንግስት ገቢን በተመለከተ

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የመንግስት ገቢ በእጅጉን ጨምሯል፡፡ ባላፉት ሶስት ወራት 180 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ ተችሏል፡፡ ይህም ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጻር የተሻለ እድገት የተመዘገበበት ነው፡፡ በ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት የተሰበሰበው ገቢ 109 ቢሊዮን ብር ብቻ ነበር፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ጥቅል ምርት አንጻር አሁንም ዝቅተኛ ገቢ የምትሰበስብ…

Read More

ሁለተኛ ቀኑን የያዘው የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀመረ

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጃነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በተገኙበት በታርጫ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል። ምክር ቤቱ በጉባኤው በመጀመሪያ ቀን ውሎ የክልሉ መንግሥት አስፈጻሚ ተቋማት የ2018 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ረፖርት ቀርበው በምክር ቤት አባላት ተገምግመው ማጽደቁ…

Read More

የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ሥራ ውጤታማ እንዲሆን የሐይማኖት ተቋማት ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ዘርፍ ለክልልና ዞን ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ አመራርና አባላት የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ የግንዛቤ መፍጠሪያ እና የጋራ የውል ስምምነት መድረክ በቦንጋ ከተማ እያካኸደ ነው። መድረኩ ዘመናዊ የህዝብ አስተዳደር ሥርዓትን ለመገንባት የሚያስችሉ የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ስርዓት በሚቀላጠፍበት ጉዳዮች ላይ ከመሪ ተዋንያኖች ጋር ለመግባባት እንደሆነ ተገልጿል። በመድረኩ ተገኝተው…

Read More

በጋምቤላ ክልል ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ምሁራን የበኩላቸውን ሃላፊነት እንዲወጡ ተጠየቀ::

በጋምቤላ ክልል አልፎ አልፎ የሚከሰተው የጸጥታ መደፍረስ በዘላቂነት እንዲፈታ ምሁራን የበኩላቸውን ሃላፊነት እንዲወጡ ተጠየቀ። በክልሉ የሚገኙ ምሁራን ከክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በወቅታዊ የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡጁሉ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት÷ የተለያዩ ከፋፋይ ትርክቶችን የሚነዙ አካላት ክልሉን የግጭት ቀጠና ለማድረግ በሰዎችና በንብረት ላይ ጉዳት እያደረሱ ነው። በፅንፈኝነት ታውረው የሰዎች ሕይወት እንዲጠፋ…

Read More

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኅን ሀገራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ አጀንዳዎች ላይ በማተኮር ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ ሊሰጡ ይገባል፦የዘርፉ ምሁራን

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኅን ሀገራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ አጀንዳዎች ላይ በማተኮር ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ ሊሰጡ እንደሚገባ የዘርፉ ምሁራን ገለጹ። መገናኛ ብዙኅን የሚያመነጯቸው መረጃዎች ግንዛቤን በመፍጠር፣የሀገር ገጽታ በመገንባት፣ ዕቅድና ፖሊሲዎችን በማስተዋወቅ ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገትና ብሔራዊ ጥቅም መጠበቅ ቁልፍ ሚና አላቸው። በዜጎች መካከል የሚንጸባረቁ በብዝኅነት ላይ የተመሰረቱ እሳቤዎች የሚስተናገዱበትን አጀንዳ በመቅረጽም አሰባሳቢ ትርክት ግንባታን በማስተጋባት ብሔራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ…

Read More

ማዳበሪያ ማምረት ከአገር ሉዓላዊነት ጋር የሚያያዝ ነው፡- የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ

ማዳበሪያ ማምረት ከአገር ሉዓላዊነት ጋር የሚያያዝ ነው፡- የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በኢትዮጵያ ማዳበሪያ ማምረት ከአገር ሉዓላዊነት ጋር የሚያያዝ ነው ሲሉ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ተናገሩ። ሚኒስትሩ በቀጣይ ለመገንባት ስምምነት የተፈረመበትን የማዳበሪያ ማምረቻ ፕሮጀክት አስመልክቶ ከኢቢሲ ጋር ቆይታ አድርገዋል። ፕሮጀክቱ ማዳበሪያን በአገር ውስጥ አምርቶ በሚፈለገው ጊዜ እና በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የአርሶ አደሩን ምርት ለማሳደግ የሚያስችል ነው…

Read More

በሸካ ዞን የጥምቀት በዓል በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በሸካ ዞን በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። በዓሉ በቅዳሴ፣ በፀሎት፣ በዝማሬ፣ በምስጋና እና በሌሎች ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። ትላንት ታቦታቱ ከመንበረ ክብራቸው ወጥተው ባደሩበት የባህረ ጥምቀት ሥፍራው ከሌሊቱ ጀምሮ ሥርዓተ ቅዳሴና ልዩ ልዩ ኃይማኖታዊ ክዋኔዎች እየተከናወኑ ያደረ ሲሆን በጠዋቱ ክፍለጊዜም የጥምቀት ስነስርዓት በካህናቱ አማካይነት ተከናውኗል። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች…

Read More

ክልሉ ያለዉን እምቅ አቅም ተጠቅሞ በዜጎች ስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ማድረግ አለበት:-የሱፐርቪዥን ቡድን::

የኢፌዲሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን ላለፉት 10 ቀናት በክልሉ ያካሄደውን ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን ግብረ- መልስ ማጠቃለያ ውይይት በቦንጋ ከተማ አካሂዷል፡፡ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ በክልሉ በወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ የተሰሩ የተገኙ ውጤቶች ለማስቀጠል ክህሎት መር ተቋማዊ ግንባታ በማጠናከር በየአካባቢ ተገንብተው ወደስራ ያልገቡ የማምራቸ እና መሸጫ ሼዶችን አጠናቆ ወደ ስራ ማስገባት…

Read More

የወተትና ስጋ ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ የተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎችን በማዳቀል ውጤታማ ሥራ እየተከናወነ ነው

የወተትና ስጋ ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ የተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎችን በማዳቀል ውጤታማ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የወተትና ሥጋ ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎች የማዳቀል ሥራ እየተከናወነ ነው፡፡ በዚህም በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሶስት ወራት 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ላሞችን ለማዳቀል ዕቅድ ተይዞ 1…

Read More