በኢትዮጵያ የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማስፋት ለቴክኖሎጂ እና አዳዲስ አሰራሮች ትኩረት ተደርጓል – ዶክተር አየለ ተሾመ::
በኢትዮጵያ የጤና አገልግሎትን ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት ቴክኖሎጂ እና አዳዲስ አሰራሮችን ማጠናከር ላይ ትኩረት መደረጉን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አየለ ተሾመ ተናገሩ። ሚኒስትር ዴኤታው ይህን ያሉት በአፍሪካ ህብረት የመሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ በሚገኘው ስምንተኛው ሀገር አቀፍ የጤና ኢኖቬሽንና ጥራት ጉባኤ ላይ ነው። ዶክተር አየለ እንደተናገሩት በኢትዮጵያ በጤና ኤክስቴንሽን፣ በወረዳ ሽግግር እና አጠቃላይ የለውጥ ስራዎች ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች ተደርገዋል።…
