በግብርናው ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለይቶ በመፍታት ምርትና ምርታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ የካፋ ዞን አስተዳደር ጥሪ አቀረበ
የዞኑ ግብርና፣ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ መምሪያ ግምገማ ነክ የንቅናቄ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በቦንጋ ከተማ አካሂዷል፡፡ በመክፈቻው ንግግር ያደረጉት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በዞኑ ያሉ አቅሞች በመለየት በግብርናው ዘርፍ የሚስተዋሉ ማነቆዎች በመፍታት ምርትና ምርታማነት ለማረጋገጥ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ልሰሩ እንደሚገባ አሳሰበዋል፡፡ የመምሪያው ሀላፊ አቶ ጋዎ አባመጫ በበኩላቸው በበጋ መስኖ ስንዴ፣ በመደበኛ…
