ቢሮው የአሰሪና ሠራተኛ ዘርፍ የአማካሪ ቦርድ ምሥረታ አካሄደ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሥራ ክህሎት ቢሮ፤ የአሰሪና ሠራተኛ ዘርፍ የአማካሪ ቦርድ ምሥረታ በቦንጋ ከተማ አካሂዷል። ከአሰሪ፣ ከሠራተኛ እና ከመንግሥት ወገን የተወጣጡ 15 አባላት ያሉት የአማካሪ ቦርድ ተሰይመው በጉባኤው ፊት ቃሌ-መሀል ፈጽመዋል። በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የቢሮው ምክትልና የአሰሪና ሠራተኛ ዘርፍ ኃላፊ ተክሌአብ ቡሎ (ዶ/ር) እንደገለጹት፥ የአማካሪ ቦርድ መመሥረት በአሰሪና ሠራተኛ መካከል የሚፈጠሩ ችግሮች…
