በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የሚሰራው ስራ ሊጠናከር ይገባል፡- የሰላም ሚኒስቴር
በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና አንድነትን ለማጠናከር የሚሰራው ስራ ሊጠናከር እንደሚገባ የሰላም ሚኒስትሩ መሐመድ እድሪስ ተናግረዋል። ሀገር አቀፍ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የጎሳ መሪዎች እና የሰላም ተቋማት አመራሮች የምክክር መድረክ በአፍሪካ የአመራር ልህቀት ማዕከል እየተካሄደ ነው። በምክክር መድረኩ የሰላም ሚኒስትሩ መሐመድ እድሪስ ኢትዮጵያ በርካታ የከበረና የዳበረ ባሕላዊ የሰላም ሐብቶች ያሏት ሀገር መሆኗን ገልጸዋል። እነዚህ ሐብቶች ግጭቶችን…
