በክልሉ የማይነጥፍና ፍትሃዊ የንብረት ግብር ለመሰብሰብ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ግመታና አሰራር ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል፦ ወ/ሮ ሄለን ደበበ

የኢፌዲሪ ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የሪል ስቴት ልማትና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅ ቁጥር 1357/2017 ላይ የስልጠና መድረክ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል፡፡ የስልጠና መድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ የኢፌዲሪ ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስተር ዴኤታ ወ/ሮ ሄለን ደበበ በሪል ፕሮፐርቲ ግመታና ግብይት ወጥነት ያለው ስርዓት ለመዘርጋት እና የከተሞችን የፋይናንስ አቅም ለማሳደግ ገቢ አሰባሰብ ላይ የሚፈለገውን መሠረታዊ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግሥት ከኦሮሚያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ጋር የትብብር ስነድ ተፈራረመ

የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልል መንግሥት፤ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችል የጋራ ውይይት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾና የክልሉ የካቢኔ አባላት በተገኙበት አድርገዋል። በሁለቱ አጎራባች ክልሎች ለዘመናት የዘለቀው ጠንካራ ማህበራዊ መስተጋብር እንዲሁም የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እንዳለ ያወሱት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ይህን መልካም ግኑኝነት ወደ ልማት…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በቦንጋ ከተማ ጥራታቸው የተጠበቁ እና የዘር ምንጫቸው የታወቁ የአትክልት ዘሮች እና ሌሎች ኬሚካሎች ለኤግዚቢሽን ቀረበ

በኤግዚቢሽኑ በርካታ ካምፓኒዎች የተሳተፉ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ማርቆስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የተለያዩ አትክልት ዘሮች፣ ሚኢረጅ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የጸረ አረምና ጸረ ተባይ ኬሚካል የኬምቴክስ የግብርና ምርቶች፣ ዋይዝ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት የአትክልት ዘር፣ እንዲሁም ሌሎች የተለያዩ ድርጅቶች ምርቶቻቸውን ለእይታ አቅርበዋል። በኤግዚብሽኑ ምርቶቻቸውን ይዘው የቀረቡ የተለያዩ ድርጅቶች ለምርትና ምርታማነት ማደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸው ምርቶችን…

Read More

ለውጡን ተከትሎ በግብርና ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገሩ ናቸው – ግርማ አመንቴ(ዶ/ር)

ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በግብርና ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገሩ መሆናቸውን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለፁ። ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በግብርና ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ÷ በዘርፉ መዋቅራዊ ሽግግርን ማምጣት የሚያስችሉ ሥራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል። በተለይ የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴንና የሜካናይዜሽን እርሻን የማስፋት እንዲሁም በዝናብ ላይ ጥገኛ የነበረውን ግብርና በመቀየር ዓመቱን ሙሉ ወደ…

Read More

በ2016 ዓመተ ምህረት የምርት ዘመን የስንዴ ምርት በምን ያህል ከፍተኛ ደረጃ ማደጉን ያውቁ ይሆን?

አነስተኛ ማሳ ተጠቃሚ ገበሬዎች 3.6 ሚሊዮን ሄክታር አርሰው 123 ሚሊዮን ኩንታል ሲያመርቱ በመስኖ ከታረሰው 2.9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ደግሞ 107.7 ሚሊዮን ኩንታል ማምረት ተችሏል። የ2016 የኢትዮጵያ የስንዴ ምርት በድምሩ 230 ሚሊዮን ኩንታል ደርሷል። ከ2012 የምርት ዘመን ጋር ሲነፃፀር አነስተኛ ማሳ ተጠቃሚ ገበሬዎቹ 54 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ብቻ ነበር ያመረቱት። ዛሬ ይህ ቁጥር ትርጉም ባለው መጠን…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የ2018 በጀት ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቦንጋ ከተማ እያካኸደ ነው።

የምክክሩ መነሻ ነጥቦች ዙሪያ ማብራሪያ የሰጡት የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር ካሳ ውይይቱ በዋናነት ባለፉት 6 ወራት የተሰሩ ተግባራት አፈጻጸም ታይተው ለተቀሩት ተግባራት ጠቋሚ ነጥቦች ላይ ማብራሪያ እንደሚሰጥ ገልጸዋል። ኮሚሽነሩ አክለው እንደ ገለጹት ባለፉት ጊዜያት ከክልል እስከ ወረዳና ከተማ አስተዳደር ለተቋሙ የተሰጠውን ተልዕኮ መሠረት ያደረጉ የግምገማ አፈጻጸም እንዲገለጹ ይደረጋል ብለዋል። በወንጀል መከላከል ዘርፍ የመዝገቦች ምርመራ…

Read More

ርዕሰ መስተዳድሩ ለምክርቤቱ አባላት ባቀረቡት የ6 ወራት የአፈጻጸም ሪፖርት በመሠረተ ልማት ዘርፍ ከተከናወኑ ተግባራት መካከል የሚከተሉትን ነጥቦች አንስተዋል ፡፡

የአርብቶና ከፊል አርብቶ አደር ልጆችን በሆስቴሎች 179 ተማሪዎች ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ መሆናቸው በአርብቶ አደር አካባቢ የሚታየውን የተማረ የሰው ኃይል እጥረት ለመቅረፍ በመጀመሪያ ዲግሪ 116 እና በዲፕሎማ 42 ተማሪዎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ መሆኑ በአነስተኛ የመጠጥ ውሃ ስራዎች የምንጭ ግንባታ ቤሮ ወረዳ ሲሪት ቀበሌ፣ ሜ/ሻሻ ወረዳ ቂራ ቀበሌ፣ ሜ/ሻሻ ወረዳ ጎሪነሱ ቀበሌ፣ ሜ/ሻሻ ወረዳ ቦኡት ቀበሌ 100% የተጠናቀቁ…

Read More

በግብርናዉ ዘርፍ የተገኙ ዉጤቶች:-

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የግብርና ዘርፉ 7 ነጥብ 3 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል፤ የግብርናው ዘርፍ በአጠቃላይ የኢኮኖሚ እድገት ውስጥ 2 ነጥብ 3 በመቶ ድርሻ አበርክቷል፤ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ የግብርናው ዘርፍ ከፍተኛ እድገት አስመዝግቧል፤ በ2010 ዓ.ም የሩዝ ምርት 1 ነ ጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል የነበረ ሲሆን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 63 ሚሊዮን ኩንታል ማድረስ ተችሏል፤ በስንዴ ምርት በለውጡ…

Read More

ከቡናው ዘርፍ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ቡና፣ሻይና ቅመም ባለስልጣን ከክልሉ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም የበጀት ድጋፍ በቡና ዕሴት ሰንሰለት ዙሪያ በተደረገ ጥናት ውጤት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ በቦንጋ እየተካሄደ ይገኛል ። መድረኩን በመክፈቻ ንግግር የከፈቱት የክልሉ ቡና ፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አስራት መኩሪያ የመድረኩ ዓላማ በተለዋዋጭ ዓለም ውስጥ በቡናው…

Read More

በአዳማ የተጀመረዉ የስማርት ሲቲ ግንባታ ቀልጣፋ መንግሥታዊ አገልግሎት መስጠት ማስቻሉ ተገለጸ

“ዓላማ ተኮር፣ የተናበበ እና የተቀናጀ የተግባቦት ሥርዓት ለእመርታዊ ዕድገት” በሚል መሪ ሐሳብ እየተካሄደ ያለዉ የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ የጋራ ጉባኤ ተሳታፊዎች የአዳማ ከተማን “ስማርት አዳማ ፕሮጀክትን” ጎብኝተዋል፡፡ የከተማዋ የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ የመንግሥትን አሠራር ሥርዓት ከማዘመኑም በላይ ለማኅበረሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ያስቻለ መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር ) ገልጸዋል፡፡ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተሠሩ ያሉ…

Read More