Trendings

Getenesh Gebeyehu

የክልሉ የድጋፍና ክትትል ቡድን በካፋ ዞን የተለያዩ ወረዳዎችና በአንድ ከተማ አስተዳደር ድጋፋዊ ክትትል ያደረገው ቡድን ግብረ-መልስ አቅርቧል::

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር የማታለም ቸኮል የድጋፍና ክትትል ግብር- መልስ ሪፖርት አቅርበዋል ፡፡ የደጋፍና ክትትል ዓላማው በሁሉም መስኮች የተመዘገቡ አበረታች ተግባራትን አጠናክሮ ማስቀጠልና ጉድለቶችን ፈጥኖ ማረም የሚያስችል አቅጣጫ ማስቀመጥ መሆኑን ተናግረዋል ፡፡ በፖለቲካው፣በኢኮኖሚ፣በማህበራዊ እና በአስተዳደር ዘርፎች በተከናወኑት ሥራዎች የተመዘገቡ አበረታችና ተስፋ ሰጪ ውጤቶችንና ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን ዘርዝረዋል ፡፡…

Read More

ለውጡ ዜጎች በሀገራቸው የፓለቲካ ጉዳይ ላይ ያለከልካይ መሳተፍ አለባቸው የሚለውን እሳቤ ያመጣ ነው፦ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)

ያለፉት 7 የለውጥ ዓመታት ዜጎች የሀገራቸው የፓለቲካ ጉዳይ ላይ ያለከልካይ መሳተፍ አለባቸው የሚለውን እሳቤ ያመጣ ነው ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ዓለም አቀፍና የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለፁ። ለውጡ የአጋር እና የዋና ፓርቲ ክፍፍልን በማስቀረት ህብረ ብሄራዊ፤ ሀገራዊ ፓርቲ በመመስረት ዜጎች በሀገራቸው ጉዳይ ግንባር ቀደም ተሳታፊ እና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረጉንም ጠቅሰዋል። ሀገር ውስጥም ሆነ…

Read More

የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ እና ኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን ቢሮ የትራንስፖርት አገልግሎትን ዲጂታል ለማድረግ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ

የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ከክልሉ ኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን ቢሮ ጋር በመተባበር የትራንስፖርት ዘርፉን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሳደግ ቴክኖሎጂን መጠቀም ዙሪራ ውይይት አደርገዋል። በፊርማ ስነስርዓቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ መሠረተልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጂዎ ሳፒ በህዝብ ትራንስፖርት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ዲጂታል መፍትሄዎችን መቀበል ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል። የትራንስፖርትና መንገድ ልማት…

Read More

በዕውቀት፣ በክህሎትና በስነ ምግባር የታነፀ የፖሊስ አመራሮችና አባላትን ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ከፌደራል ፖሊስ እና ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩንቨርስቲ ጋር በመቀናጀት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ለሚወስዱ አመራሮች በቦንጋ ከተማ ስልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ በሰላም ማስከበር ስልጠና ማስጀመሪያ ላይ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሰብስቤ ሻዌኖ የህዝብ ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ዕውቀትና ስነ ምግባርን የተላበሰ ፖሊስ እና ዘመናዊ የፖሊስ ተቋምን…

Read More

በክልሉ ህጋዊ ሰውነት ኑሯቸው ከሚንቀሳቀሱ ሀገራዊም ሆነ ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተቀናጅቶ እየተሰራ ያለውን ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል፦ አቶ ፍቅሬ አማን

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤና የቀጣይ አቅጣጫ የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን እንደገለፁት በሀገራችን ያሉ የፓለቲካ ፓርቲዎች ለሀገር ሠላም፣ልማት ፣አብሮነት፣ የጋራ የሚያደርጉ ጉዳዮች ላይ በጋራ በመስራት ይዘውት የተነሱበትን ዓላማ ለማሳካት መንቀሳቀስ ይገባል ብለዋል። በሀገር በቀል የፖለቲካ እሳቤዎችን…

Read More

ለውጡን ተከትሎ በግብርና ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገሩ ናቸው – ግርማ አመንቴ(ዶ/ር)

ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በግብርና ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገሩ መሆናቸውን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለፁ። ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በግብርና ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ÷ በዘርፉ መዋቅራዊ ሽግግርን ማምጣት የሚያስችሉ ሥራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል። በተለይ የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴንና የሜካናይዜሽን እርሻን የማስፋት እንዲሁም በዝናብ ላይ ጥገኛ የነበረውን ግብርና በመቀየር ዓመቱን ሙሉ ወደ…

Read More

advd

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በ6ኛው ዙር ስልጠና የሚወስድ 50 ሰልጣኝ ዲፕሎማቶች ስልጠና አስጀምሯል። በስልጠና ማስጀመሪያው የሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ንጉስ ታደሰ እንዳሉት ፣ ዩንቨርስቲው በዲፕሎማሲ ዘርፍ በቂ ስልጠና መስጠት የሚያስችል አቅምና ልምድ አለው። ዩኒቨርስቲው ዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል ከፍቶ ተማሪዎችን እያሰለጠነ ይገኛል ብለዋል። ሰልጣኝ ዲፕሎማቶችም ዓለም አቀፍ ነባራዊ ሁኔታን መረዳት የሚያስችል እውቀት ይዘው…

Read More

በኢቢኤስ የተላለፈው የሀሰት መረጃ በሀገሪቱ ግጭት ለማስፋፋት ያለመ መሆኑ ተነገረ

ከሰሞኑ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ብርቱካን ተመስገን በተባለች ግለሰብ ዙሪያ የተሰራው የተቀነባበረ የሀሰት ዘገባ ግጭት ለማስፋፋት ያለመ መሆኑን መገንዘባቸውን ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ያነጋገራቸው የሐረር ከተማ ነዋሪዎች ተናግረዋል። ሀሳባቸውን ከሰጡ የከተማው ነዋሪዎች መካከል ወጣት ሙራድ አብዲ የቀረበው የሀሰት ዘጋቢ ፊልም ህዝብን በሀሰት መረጃ ለማሳሳት እየተሰራ እንደሆነ የሚያሳይ መሆኑን ገልጿል። እንዲህ አይነት ድርጊት ሀገርን የሚጎዳ በመሆኑ የማያሳዝንና ተቀባይነት የሌለው…

Read More

በክልላችን በወኃ፣ በመስኖ ልማት እና በማዕድን ዘርፍ የተገኙ አመርቂ ውጤቶች የመጋቢት 24 ፍሬዎች ናቸዉ፦ ኢንጂነር በየነ በላቸው

የመጋቢታዊያን የለውጥ ትሩፋቶችን አስመልከቶ የክልሉ የውኃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር በየነ በላቸው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በዉሃ፣በመስኖና በማዕድን ዘርፍ የተመዘገቡ ድሎችን የዕይታ ለውጥ እና ሽግግርን ጭምር ያመጡ መሆናቸዉን ገልጸዋል ። ኢንጂነር በየነ በመግለጫቸው ከለውጡ በፊት ዘርፉ እንደሀገር ብዙ ትኩረት ያልተሰጠበት መሆኑን በማስታወስ አሁን ዕምርታዊ ለውጥ መምጣቱን በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ የተሰጠው ትኩረት በርካታ የውጭ…

Read More

ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ በግብርናው ክፈለ-ኢኮኖሚ በርካታ ለዉጦች ተመዝግበዋል። አቶ ማስረሻ በላቸው

ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ በግብርናው ክፈለ-ኢኮኖሚ በርካታ ለዉጦች መመዝገባቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተደድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው የሰባት ዓመታት የለውጥ ጉዞና የተገኙ ትሩፋቶችን በሚመለከት በጽ/ቤታቸው ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግልጫ ሰጥተዋል። መጋቢት 24/2010 ዓ/ም የለውጡ መንግሥት ወደ መንበረ ስልጣን ሲመጣ፥ ሀገሪቱ ዘርፈብዙ ችግሮች ውስጥ እንደነበረች ያወሱት…

Read More