Trendings

Getenesh Gebeyehu

የፓርላማና የፌዴሬሽን ም/ቤት የልዑካን ቡድን በዓለም አቀፉ ፓርላማ ህብረት ጉባኤ ላይ እየተሳተፈ ነው

በፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር የተመራው የፓርላማና የፌዴሬሽን ምክር ቤት የልዑካን ቡድን በኡዝቤኪስታን ታሽከንት ከተማ እየተካሄደ ባለው በ150ኛው በዓለም አቀፉ ፓርላማ ህብረት (አይፒዩ) እየተሳተፈ ይገኛል። በመድረኩ ኢትዮጵያን በመወከል ንግግር ያደረጉት አፈጉባዔ አቶ አገኘሁ ተሻገር፤ ኢትዮጵያ በህብረቱ ላይ ያላትን አጋርነት አጠናክራ ለመቀጠል ቁርጠኛመሆኗን ገልጸዋል። ለ2030 የዘላቂ ልማት ግቦች ስኬት የሚመለከታቸው አካለት ዓለም አቀፍ…

Read More

በኤች አይቪ ህክምና ላይ ያሉ ሰዎች የቫይረስ መጠን ልኬት አፈጻጸም ለማሳደግ በተሰጠው ትኩረት ውጤት እየተመዘገ ነው።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ፥ ከጤና ሚኒስቴር እና አይካፕ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የቫይረስ መጠን ልኬት እና ተጋላጭ የጨቅላ ህጻናት ምርመራ የ2017 በጀት ዓመት ስምንት ወር አፈጻጸም ዙሪያ የተዘጋጀ የጋራ ምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። ባለፉት 8 ወራት የፀረ-ኤች አይቪ ህክምና ላይ ያሉ ሰዎች የቫይረስ መጠን ልኬት ሽፋን ለማሳደግ በተሰጠው ትኩረት…

Read More

የክልሉ ውሀ፣ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀምና የቀሪ 3 ወራት የትኩረት አቅጣጫ ላይ የምክክር መድረክ በቦንጋ እያካሄደ ነው።

በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ በዘርፉ የመጣው ለውጥ አመርቂ መሆኑን በማንሳት አሁንም ከግማሽ በላይ የሆነ የክልሉ ህብረተሰብ ክፍል የንጹህ መጠጥ ውሃ እጥረት ያለበት በመሆኑ በቁርጠኝነትና በቅንጅት መፍጠርና መፍጠንን በማከል መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል። የውሃ ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ በፍትሐዊ መንገድ ተደራሽ በማድረግ በየደረጃው ከህብረተሰቡን የሚነሱ ቅረታዎችን በመፍታት መልካም…

Read More

አገልግሎት አሰጣጥን ፍትሃዊና ቀልጣፋ በማድረግ የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ

አገልግሎት አሰጣጥን ፍትሃዊና ቀልጣፋ በማድረግ የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍና የህብረተሰቡን እርካታ ማረጋገጥ በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ ለሸካ ዞን አጠቃላይ አመራር፣ለወረዳና ከተማ አስተዳደር አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት በቴፒ ከተማ ኦረንቴሽን ተሰጥቷል። ለአመራሩ ኦረንቴሽኑን የሰጡት የሸካ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የዞኑ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ አለሙ በወቅቱ እንደተናገሩት በርካታ ተቋማት አካባቢ ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ ሰፊ…

Read More

የሸካ ህዝቦች ልማት ማህበር 11ኛ ጠቅላላ ጉባኤ በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ መካሄድ ጀምሯል

በጉባኤው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የልማት ማህበሩ የበላይ ጠባቂ አቶ አበበ ማሞ እንደገለፁት በጉባኤው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የሸካ ህዝቦች ልማት ማህበር ግንቦት 16/1985 ዓ.ም ከተመሰረተ ጊዜ አንስቶ ህብረተሰቡን፣ መንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን በማስተባበር የዞኑን የልማት ፍላጎት የመደገፍ ስራዎች በመስራት ላይ መሆኑን ተናግረዋል። ማህበሩ በእስካሁን ጉዞው በጤና ፣ በትምህርት ፣በመንገድ ግንባታ ፣ በባህል…

Read More

የውሃ መስኖና ኢነርጂ ዘርፍ የዜጎችን መሠረታዊ ፍላጎት ከማሟላትም ባሻገር ለሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ ከፍተኛ ሚና አለው፦ አቶ ነጋ አበራ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የውሃ ማዕድን እና ኢነርጂ ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀምና ጉባኤና የቀሪ 3 ወራት የትኩረት አቅጣጫ ላይ የምክክር መድረክ በቦንጋ እያካሄደ ነው። በጉባኤው የተገኙት የክልሉ የመንግስት ረዳት ተጠሪና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ ክልሉ ከተመሠረተ ወዲህ በዘርፉ ለውጥን ሊያመጡ የሚያስችሉ በርካታ መሠረታዊ ዕድገት ተኮር…

Read More

3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው

ሦስተኛው የፓርላማ የዜጎች ፎረም “ሕገ መንግሥትና ሕገ መንግሥትታዊነት በኢትዮጵያ” በሚል መሪ ሐሳብ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እየተካሄደ ነው፡፡ በውይይቱ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ በምክር ቤቱ የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የምክር ቤት አባላት፣ ምሁራንና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ የኢትዮጵያ እና የዓለም ሕገ-መንግሥቶች የታሪክ ጉዞ ላይ ያተኮሩ ጽሑፎችም በፎረሙ ላይ…

Read More

የህብረት ሥራ ዘርፍ ሚናዉን በአግባቡ እንዲወጣ ወደ ሪፎርም ሥራ መግባቱ ተገለጸ

የክልሉ ህብረት ስራ ልማት ኤጀንሲ የ9 ወር ዕቅድ አፈጻጸም እና የህብረት ስራ ማህበራት ሪፎርም አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በሚዛን አማን እየተካሄደ ይገኛል። የክልሉ የአካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ ኃላፊና ኢንጂነር አስራት ገብረማሪያም (ዶ/ር) መድረኩን በንግግር ሲከፍቱ እንደተናገሩት የህብረት ስራ ማህበራት በአለምና በሀገራት ኢኮኖሚና የዜጎችን ህይወት በመቀየር ረገድ ጉልህ ሚና አበርክተዋል ብለዋል። ከሀገራዊ ለውጡ ማግስት እንደ…

Read More

የግብርና ኤክስቴንሽን የምክር አገልግሎትን ፈጣን ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ በማድረግ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተገለጸ

የክልሉ ግብርና ቢሮ የተሳትፏዊ ግብርናና የአየር ንብረት ሽግግር ፕሮግራም (Pact Programme) ለአርሶ አደር መስክ ትምህርት ቤት አመቻቾች ስልጠና በሚዛን አማን እየተካሄደ ይገኛል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ የተሳትፏዊ ግብርናና የአየር ንብረት ሽግግር ፕሮግራም ስራ አስኪያጅ አቶ ታመነ ተስፋዬ እንደተናገሩት ፕሮግራሙ በክልሉ በሴፍትኔት በታቀፉ ዞኖችና ወረዳዎች ላይ የሚሰራ መሆኑን ገልጸው በዚህም በምዕራብ ኦሞ ዞን…

Read More

በክልሉ በፌደራል መንግሥት የሚገነቡ የአስፓልት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታዎች ላይ የሚታየዉ የአፈጻጸም ችግር ሊታረም እንደሚገባ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ አሳሰቡ

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከኢፌዲሪ ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር አዲስ በተሻሻለው የካሳ አዋጅ ቁጥር 1336/2016 ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እና በክልሉ በፌደራል መንግሥት የሚገነቡ የመንገድ ፕሮጀክቶች ያሉበት ደረጃና የክልሉን ድጋፍ የሚሹ ጉዳዮች ዙሪያ በክልሉ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተወያይተዋል። አዲስ ተሻሽለው የወጣዉ የካሳ አዋጅ ንብረት የመገመት፣ የመክፈል እና የማስነሳት ስራ ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት የሚያግዝ…

Read More