የትምህርት ሚኒስቴር የብርቱካን ተመስገን ከበደ ጉዳይን በተመለከተ የሰጠው መግለጫ
ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ስለሆነችው ብርቱካን ተመስገን ከበደ ከትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠ ማብራሪያ ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ስለሆነችው ብርቱካን ተመስገን ከበደ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር ግንኙነት ስላለው ማብራሪያ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። በስም ተጠቃሽ በ2012 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪ የነበረች ቢሆንም የብሄራዊ ፈተናው በወቅቱ በተፈጠረው ዓለም ዓቀፍ የኮቪድ ወረርሽኝ ምክንያት ከየካቲት 29 እስከ መጋቢት 02/2013 ዓ.ም…
