Trendings

Getenesh Gebeyehu

ኢትዮጵያ ለስታርት አፕ እድገት ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር በትኩረት እየሰራች ነው – በለጠ ሞላ (ዶ/ር)

በኢትዮጵያ የስታርት አፕ እድገትን የሚያሳልጥ ምቹ ምሕዳር ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል። በኢትዮጵያ ለስታርት አፕ እድገት ተቋማዊና ሕጋዊ አሰራርን የሚዘረጋ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ውይይት ቀርቦ ምክክር እየተደረገበት ነው። የረቂቅ አዋጁ ዓላማ ለስታርት አፕ ተቋማዊና ሕጋዊ ድጋፍን በመስጠት በኢትዮጵያ የዘርፉን እድገት ማሳለጥ መሆኑ ተገልጿል። በስታርት አፕ ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችን መፍታትና የፋይናንስ አቅርቦትን ማመቻቸትም…

Read More

የቡና ምርታማነትና ጥራት በማሻሻል ከዘርፉ የሚገኘዉን የዉጭ ምንዛሬ ለማሳደግ በትኩረት እየሰራን እንገኛለን። ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር ኢ/ር)

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቡና ምርታማነትና ጥራት ማሻሻያ ላይ ትኩረት ያደረገ የንቅናቄ መድረክ በሚዛን አማን እየተካሄደ ይገኛል በንቅናቄው መድረክ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ክልሉ ከፍተኛ ቡና የማምረት አቅም ያለዉ መሆኑን ጠቅሰዉ በምርታማነትና በጥራት ላይ በመስራት የህብረተሰቡንም ሆነ የሀገርቱን ከኢኮኖሚ ከማሳደግም ባሻገር ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እያመጣ እንደሆነ አንስተዋል ።…

Read More

ብልፅግና ፓርቲ በጥቂት ዓመታት መልከ ብዙ ስኬቶችን ዕውን ያደረገ ፓርቲ ነው – አቶ አደም ፋራህ

ብልፅግና ፓርቲ በጥቂት ዓመታት ውስጥ መልከ ብዙ ስኬቶችን ዕውን ማድረግ የቻለ ፓርቲ መሆኑን የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንትና በም/ ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊ አደም ፋራህ ገለጹ፡፡ የብልፅግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምስረታ በዓል “የሃሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልፅግና” በሚል መሪ ሃሳብ በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተከበረ ነው። አቶ አደም ፋራህ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ÷ብልጽግና በሃሳብ…

Read More

የብልጽግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት ምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ የጽዳት ዘመቻ ተደረገ

የብልፅግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን አስመልክቶ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦቸች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ አመራሮችና አባላት በቦንጋ ከተማ የፅዳት ዘመቻ ተካሂዷል። በመርሀ ግብሩ የክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ሰብለጸጋ አየለ እንደገለፁት የዛሬው የጽዳቱ ዋና አላማ የብልፅግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን አስመልክቶ የተዘጋጀ የጽዳት ፕሮግራም መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለነዋሪዎች ውብና የተመቸ…

Read More

በክልሉ ጥራትና ብቃት ያላቸውን መምህራን አሰልጥኖ ወደ ስራ ለማሰማራት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን የትምህርት ቢሮ ገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ በክልሉ ጥራትና ብቃት ያላቸውን መምህራን አሰልጥኖ ወደ ስራ ለማሰማራት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ አልማው ዘውዴ ገልጸዋል። ትምህርት ቢሮው ከቦንጋ ትምህርት ኮሌጅ ጋር በመተባበር በ2017 የትምህርት ዘመን በዲፕሎማና በሰርተፍኬት መርሃግብር 730 ዕጩ መምህራንን ተቀብሎና በብቃት አሰልጥኖ ወደ ስራ…

Read More

አልሚ ባለሀብቶች የሜካናይዜሽን እርሻዎችን በማጠናከር ጥራትና እሴት ጨምረው ማልማት ይገባቸዋል ።ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

በግብርና ኢንቨስትመንት ስራዎች ስትራቴጂክ በሆኑ የገበያ ምርቶች ላይ ትኩረት በማድረግ መስራት እንደሚገባ ተገልጿል ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ የምግብ ሥርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም( FSRP) ጋር በመተባበር ክልል አቀፍ የግብርና ኢንቨስትመንት ባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ በቦንጋ ከተማ አካሂዷል ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ከ3.91 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት እንደሚገኝ የክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ መረጃ…

Read More

ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት አምስት ዓመታት ባከናወናቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት አኩሪ ድሎችን ማስመዝገብ ችሏል ፦አቶ ነጋ አበራ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ የብልጽግና ፓርቲ 5ተኛ ዓመት ምስረታ በዓል አከባበር ዙሪያ አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል። የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ በመግለጫቸው ፓርቲያችን የሀሳብ ፓርቲ እንደመሆኑ መጠን የሀሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል 5ኛ ዓመት…

Read More

የብልጽግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች በሸካ ዞን ተከበረ

የሸካ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የሀሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በልዩ ልዩ ዝግጅት በደማቅ ሁኔታ በቴፒ ከተማ እየተከበረ ይገኛል። በበዓሉ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የዞኑ በብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ አለሙ እስካሁን የተመዘገቡ ስኬቶችን በማስፋትና ክፍተቶችን በማረም ለሁለንተናዊ ብልፅግና መረጋገጥ መትጋት ያስፈልጋል ብለዋል። ለብልፅግና ፓርቲ 5ኛ…

Read More

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂን በአግባቡ በመጠቀም ምርትና ምርታማነት የሚያሳድግ አርሶ አደር መፍጠር እንደሚገባ ተገለፀ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ጋር በመተባበር የ2017 ዓ.ም የበጋ መስኖ ልማትን በተመለከተ ለዞንና ለወረዳ ግብርና ባለሙያዎች በቦንጋ መዕከል የክህሎት ስልጠና ይገኛል፡፡ የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ክንፉ በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ እንደገለጹት፣ ክልሉ በሶስት ምርት ወቅቶች ላይ ሰብል የሚያመርት መሆኑን ገልጸው ከዚህም አንፃር በአንደኛ እና…

Read More

በቦንጋ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እና የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያተኮረ የህዝብ አስተያየት መስጫ መድረክ እየተካሄደ ነው።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት በቦንጋ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እና የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያተኮረ የህዝብ አስተያየት መስጫ መድረክ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። የክልሉ ምክር ቤት ከተማና መሠረተ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ አሰገደች ወልደየስ በመድረኩ እንደገለጹት አስፈጻሚ ተቋማት የሚያከናውትን ተግባራት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንዲሁም ክፍተቶች ሲኖሩ የህዝብ አስተያየት መውሰድ…

Read More