Trendings

የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደቱ ግለፀኝነትና አሳታፊ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮች ገለፁ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል እየተከናወነ ያለውን 3ኛ ቀኑን የያዘውን የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ አስመልክቶ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በቦንጋ ከተማ መግለጫ ሰጥቷል። በመግለጫው ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሉጌታ አጎ የእስካሁን ያለውን የምክክሩን ሂደት ከሁሉም ወረዳዎች የተመረጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ወኪሎች ግልጽና አሳታፊ በሆነ መልኩ አጀንዳቸውን አደራጅተው ያጠናቀቁበት የምክክር መድረክ መሆኑን ገልፀዋል። በክልሉ የህብረተሰብ ወኪሎች…

Read More

ሀገራዊ ሪፎርም ከተጀመረ በኋላ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ የመጠባበቂያ ክምችት በእጥፍ አድጓል

ሀገራዊ ሪፎርም ከተጀመረ በኋላ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ የመጠባበቂያ ክምችት በእጥፍ ማደጉን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምሕረቱ አስታወቁ፡፡ አዲሱ የብሔራዊ ባንክ ማሻሻያ አዋጅ ከዚህ ቀደም ለረዥም ዓመታት ሲሠራበት የቆየውንና ለዋጋ ንረት ዋና መነሻ ነበር ሲባል በቆየው አሠራር ላይ ጠበቅ ያለ የማሻሻያ ድንጋጌ ይዞ መቅረቡን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምሕረቱ ከሴንትራል ባንኪንግ መጽሔት ጋር ባደረጉት…

Read More

የ’World Without Hunger’ ጉባኤ ተሳታፊዎችን እንኳን ወደ አፍሪካ የዲፕሎማሲ መዲና በሰለም መጣችሁ እላለሁ።

አለምአቀፍ መሪዎችን፣ ባለሞያዎችን እና የጉዳዩ ተቆርቋሪዎችን በአንድ ላይ በማምጣት እንዲወያዩ በማድረግ የጋራ ጥረቶቻችን ረሃብን በማጥፋት ለሁሉም የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ርብርብ ፍሬ እንዲያፈራ እንደሚያስችሉ ተስፋ አለኝ። በኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ዓመታት በግብርና ሽግግር እና ምርታማነት ላይ በማተኮር የሠራነው ሥራ የታረሰ መሬታችን እጥፍ በማድረስ ከፍ ያለ እሴት ባላቸው የኢንደስትሪ አዝርዕት ምርት ላይ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች አስገኝቷል። በሚቀጥሉት ቀናት…

Read More

የክልሉ ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በተጨባጭ እንዲረጋገጥ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በመቀራረብ እየተሰራ ነው፦አቶ ነጋ አበራ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግሥት ፋይናንስ ቢሮ እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የ3ኛ ዙር የጋራ ምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ነው። በምክክር መድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ መንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ነጋ አበራ የክልሉ መንግስት ፈጣንና ቀልጣፋ የልማት ስራዎችን ለህዝቡ ተደራሽ ለማድረግ በርካታ የአሰራር ስርዓቶችን በመዘርጋት እየሰራ እንደሆነ ጠቁመዋል። በዚህም የክልሉ ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት…

Read More

ሀገራዊ ምክክሩ በሀገራችን እስከአሁን የነበሩ ችግሮች በንግግርና በምክክር ለመፍታትእጅግ ጠቃሚ ነው፦ አስተያየት ሰጪ መምህራንና የመንግሥት ሠራተኞች

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትናንት ጥቅምት 24/2017 ዓ.ም በጀመረው አጀንዳ ማሰባሰቢያና ተወካይ መረጣ መድረክ እየተሳተፉ የሚገኙ በክልሉ ከሁሉም ዞኖች የተወጣጡ የማህበረሰብ ክፍሎች ከትላንት ከሰዓት ጀምረው አጀንዳዎቻቸውን በቡድን ሲያደራጁ ቆይተዋል፡፡ በመድረኩ እየተሳተፉ የሚገኙ መምህራንና መንግሥት ሠራተኞች የምክክር ሂደቱ የሀሳብ የበላይነትንና ነፃነትን ለማረጋገጥ እጅግ ጠቃሚ መሆኑን ተናግረዋል ፡፡ ከተሳተፉት መምህራን መካከልም መ/ር ንጉሴ ዓለሙ ከካፋ ዞን…

Read More

የወረዳ የማህበረሰብ ወኪሎች በአጀንዳዎቻቸው ላይ እየተወያዩ ነው፡፡

#ደቡብ_ምዕራብ_ኢትዮጵያ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የምክክር መድረክ እየተሳተፉ የሚገኙ የማህበረሰብ ወኪሎች ከትላንት ጥቅምት 24/2017 ዓ.ም ከሰዓት ጀምረው ከወከሉት ማህበረሰብ ይዘዋቸው የመጡ አጀንዳዎችን በውይይት በማደራጀት ላይ ናቸው፡፡ በዚህ የምክክር መድረክ ከ57 የክልሉ ወረዳዎች የተወጣጡ 1003 የሚሆኑ የዘጠኝ የማህበረሰብ ክፍል ወኪሎች በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡ እነዚህ የወረዳ የማህረሰብ ክፍል ወኪሎች ምክክራቸውን እስከ ነገ ማክሰኞ ጥቅምት 26/2017 ዓ.ም ድረስ…

Read More

ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ ለደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ የቦርድ አመራር ምደባ ሰጡ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት በወጣ አዋጅ የተቋቋመዉ የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ምደባ ሰጥተዋል። በዚህ መሠረት 1.አቶ ጸጋዬ ማሞ …..ሰብሳቢ 2.አቶ ነጋ አበራ…….ም/ሰብሳቢ 3.አቶ ፋጂዮ ሳፒ…… አባል 4.አቶ የሺዋስ ዓለሙ….አባል 5.አቶ አንድነት አሸናፊ….አባል 6.አቶ ንጉሴ ወ/ጊዮርጊስ…….አባል የሚዲያ ኔትወርክ የቦርድ አመራር ሆነዉ ተመድበዋል።

Read More

ኢትዮጵያ ያዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ ተከፈተ

ኢትዮጵያ ያዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ ተከፍቷል። ይህንን ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ፣ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ አንዱዓለም እና የመሀመድ ቢን ዛይድ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ዶክተር ከሊፋ ሙባረክ ከፍተውታል። በኮንፈረንሱ ላይ ከ16 ሀገራት የተውጣጡ የሃይማኖት አባቶችና የተቋማት መሪዎች እየተሳተፉ ነው። ኮንፈረንሱ በልዩ ልዩ መርሀ ግብሮች እስከ ነገ…

Read More

ዲጂታል ኢትዮጵያ ዕውን እንዲሆን የሳይበር ደህንነትን የማረጋገጥ ስራ በትኩረት እየተሰራ ነው -የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር

ዲጂታል ኢትዮጵያ ዕውን እንዲሆን የሳይበር ደህንነትን የማረጋገጥ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ትዕግስት ሀሚድ አስታወቁ። ለ5ተኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው አገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር ዛሬ በድሬደዋ በፓናል ውይይት እየተከበረ ነው። በዚሁ ጊዜ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ትዕግስት ሀሚድ እንዳሉት በዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ ውስጥ የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ…

Read More

በኮንፈረንስ ቱሪዝም በዓለም ላይ ስሟን የተከለችው አዲስ አበባ እንግዶቿን ተቀብላ ለማስተናገድ ተዘጋጅታለች – ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ

በኮንፈረንስ ቱሪዝም በዓለም ላይ ስሟን የተከለችው አዲስ አበባ እንግዶቿን በድምቀት ተቀብላ ለማስተናገድ ተዘጋጅታለች ሲሉ የቱሪዝም ሚኒስትር ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ ገለፁ፡፡ ሚኒስትሯ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው፤ አዲስ አበባ በዚህ ወር ከምታስተናግዳቸው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች መካከል አንዱ የሆነው “ከርሃብ ነፃ አለም” በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ጉባኤ ነገ እንደሚጀምር ገልፀዋል። በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ ከጥቅምት 26 እስከ…

Read More