Trendings

በግብርናው ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለይቶ በመፍታት ምርትና ምርታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ የካፋ ዞን አስተዳደር ጥሪ አቀረበ

የዞኑ ግብርና፣ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ መምሪያ ግምገማ ነክ የንቅናቄ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በቦንጋ ከተማ አካሂዷል፡፡ በመክፈቻው ንግግር ያደረጉት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በዞኑ ያሉ አቅሞች በመለየት በግብርናው ዘርፍ የሚስተዋሉ ማነቆዎች በመፍታት ምርትና ምርታማነት ለማረጋገጥ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ልሰሩ እንደሚገባ አሳሰበዋል፡፡ የመምሪያው ሀላፊ አቶ ጋዎ አባመጫ በበኩላቸው በበጋ መስኖ ስንዴ፣ በመደበኛ…

Read More

የኢፌዲሪ ቡናና ሻይ ባለስልጣን በቴፒ ከተማ ቅርንጫፍ በመክፈት በቅርቡ የቡና ላቦራቶሪ እና ሰርቴፊኬሽን አገልግሎት ልጀምር መሆኑ ተገለፀ

ለቅርንጫፉ መከፈት ከፍተኛውን ድርሻ ለተወጡ አካላት በሙሉ ሸካ ዞን አስተዳደር ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል። ከኢፌዲሪ ቡናና ሻይ ባለስልጣን እና ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቡናና ሻይ ባለስልጣን የተውጣጣ የአመራሮችና ከፍተኛ ባለሙያዎች ቡድን በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ተገኝተው የቡና ቅምሻ ላቦራቶሪና ሠርተፊኬሽን ማዕከልን በቴፒ ከተማ ለመክፈት እየተደረገ ያለውን ዝግጅት ምልከታ አድርገዋል። የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ…

Read More

በመረጃ የበላይነት የያዘ ሃይልና ሀገር በሌሎች ሁኔታዎች ላይ የማሸነፍ እድሉ ሰፊ ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ

በመረጃ የበላይነት የያዘ ሃይልና ሀገር በሌሎች ሁኔታዎች ላይ የበላይነት የመያዝና የማሸነፍ እድሉ ሰፊ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ የብሔራዊ ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ በማስተርስ መርሐ ግብር ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመርቋል፡፡ በምረቃ መርሐ ግብሩ ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ፣ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፣ ሚኒስትሮችና ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። ም/ጠ/ሚ ተመስገን በምረቃ…

Read More

በአቶ አደም ፋራህ የተመራ የብልጽግና ፓርቲ የልዑካን ቡድን በቻይና የተለያዩ ተሞክሮዎችን ለመቅሰም የሚያስችል ጉብኝት አደረገ

በብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንትና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ የሚመራው የፓርቲው ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በቻይና የተለያዩ ተሞክሮዎችን ለመቅሰም የሚያስችል ጉብኝት አደረገ። ቡድኑ በግብርና ምርት ከፍተኛ ውጤት እያገኘች ባለችው ኽናን ግዛት በመገኘት በግብርና ምርታማነት፣ በኢንዱስትሪ፣ በሲቪል አቪዬሽን፣ በገጠር መንደሮች ልማትና በቅርስ፣ ባህልና ታሪክ ጥበቃ እየተከናወኑ ያሉ ውጤታማ ተግባራትን ጎብኝቷል። ቡድኑ በጉብኝቱ በግብርና መስክ በተደረጉ…

Read More

ጉልበት ቆጣቢው የሩዝ ምርት – በሸካ ዞን

መንግሥት የአገር ውስጥ ገበያ ፍላጎትን በሀገር ውስጥ ምርት ለመሸፈን ትኩረት አድርጎ እየሰራበት ካለው የብርዕ ሰብሎች አንዱ ሩዝ ነው። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልም በዘንድሮው የምርት ወቅት 13 ሺህ 452 ሄክታር መሬት በሩዝ ዘር ተሸፍኗል። በሸካ ዞን ቆይታችንም በአርሶአደሩ ዘንድ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሩዝ እርሻ ተመራጭ እየሆነ መምጣቱን መመልከት ተችሏል። በዞኑ በዘንድሮው መኸር 2 ሺህ የሚጠጋ…

Read More

የሸካ ዞንን ሰላም በማጽናት በሁሉም ዘርፎች ዉጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ ተገለጸ

የሸካ ዞንን ሰላም በማጽናት በሁሉም ዘርፎች ፊት እንዲወጣና በቀጣይ 5 ዓመታት የተያዙ የልማት ዕቅዶች ዙሪያ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በቴፒ ከተማ ውይይት ተካሂዷል የከተማ ኮሪደር ልማቶች፣የመልሶ ማልማት ፣ከተማን ለኢንቨስትመንት ማዘጋጀትና መከታተል በማህበራዊና በኢኮኖሚ ዘርፍ በተለይ አዳሪ ትምህርት ቤት በመክፈት ተወዳዳሪ ትዉልድ ለመፍጠርና በሌሎችም የልማት ሥራዎች ዙሪያ ምክክር ተካሂዷል። በመድረኩ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮዽያ ህዝቦች ክልል በምክትል…

Read More

በታሪክ ተመራማሪው አቶ አሰፋ ገብረማርያም እና በአቶ አዕምሮ ገሰሰ የተጻፈ መጸሐፍ በቦንጋ ከተማ ተመረቀ፡

መጸሐፉ የካፈቾ ህዝብ ባህል እና ታሪክ ላይ ያተኮረ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ የመጸሐፉ ደራሲ አቶ አሰፋ ገብረማርያም መጽሐፉ ሰባት ምዕራፎችና 3 መቶ 36 ገጾች ያሉት እንዲሁም የካፈቾ ባህል እና ታሪክ ላይ ያተኮረ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የካፈቾ ብሔር ማንነትን፣ የጎንጋ ህዝቦች ትስስርን፣ ጥንታዊ የካፋ መንግስት አመሰራርንና ሌሎችንም ሀሳቦች ስለማካተቱ ገልጸዋል፡፡ መጽሐፉ ለታዳጊ ደራሲዎች መነሻ እንደሚሆን ገልጸው ፤ ለህትመት እንዲበቃ…

Read More

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚያከናውነው የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ ነገ ይጀመራል

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከነገ ጀምሮ የሚካሄደውን የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረክ በተመለከተ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዘገየ አስፋው እና ኮሚሽነር ሙሉጌታ አጎ በጋራ በቦንጋ ከተማ ተገኝተው ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ኮሚሽነሮቹ በመግለጫቸው በምክክር ሂደቱ ቁልፍ ከሆኑ ተግባራት መካከል አጀንዳዎች አካታችና አሳታፊ በሆነ ሂደት የማሰባሰብ እንዲሁም በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ የሚሳተፉ ተወካዮች የማስመረጥ ተግባር በመሆኑ ለዚህም ኮሚሽኑ…

Read More

የክልሉን ሠላም በዘላቂነት ለማጽናት የሚያበረታቱ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ተናገሩ።

ይህ የተገለጸው የመልካም አስተዳደርና ህግ ጉዳዮች ዘርፍ ተቋማት የአፈጻጸም ሪፖርት በቀረበበት ነው። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የ2017 በጀት ዓመት የአንደኛው ሩብ ዓመት የአፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል። የአፈጻጸም ሪፖርቱን ያቀረቡት የርዕሰ መስተዳድሩ የመልካም አስተዳደርና ህግ ጉዳዮች አማካሪ የሆኑ አቶ አክሊሉ ከበደ የሚያስተባብሯቸውን ተቋማት የአፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል ። ባቀረቡት የአፈጻጸም ሪፖርት በየተቋማቱ የሚያበረታቱ…

Read More

ብኢትዮጵያ በሩሲያ ካዛን እየተካሄደ በሚገኘው የብሪክስ የወጣቶች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ተሳትፎ በማድረግ ላይ ነች።

በስብሰባው ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት የተውጣጣ የልዑክ ቡድን እየተሳተፈ ይገኛል። በወጣቶች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ዙሪያ የፓናል ውይይት የተካሄደ ሲሆን በመድረኩ ላይ ኢትዮጵያን በመወከል መልዕክት ተላልፏል። የልዑካን ቡድኑ ኢትዮጵያ በብሪክስ ማዕቀፍ ውስጥ የመተባበር እና የአንድነት መንፈስ እንዲጎለብት ሚናዋን በተገቢው መልኩ እንደምትወጣ ገልጿል። ልዑኩ ከስብሰባው ጎን ለጎን የካዛን ከተማ የወጣት ማዕከላት እና…

Read More