በማጂ ቱም ከተማ አ/ር የማጂ ከተማ የሶላር መብራት አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት በመስጠት እየተሰራ ነው ።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በማጂ ቱም ከተማ ለዘመናት የህዝብ ጥያቄ የሆነው ይኸው የኤሌክትሪክ አቅርቦት ጥያቄን ምላሽ ለመስጠት መንግስት ትኩረት በመስጠት እየሰራ ይገኛል ። ችግሮቹን ለመቅረፍ የሶላር ቁሳቁስ የያዙ አምስት የጭነት መኪናዎች ከአዲስ አበባ ተነስተው ማጂ ከተማ መድረሳቸውን የማጂ ቱም ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል።
