Trendings

በክልሉ የገጠር ትስስር ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና (RCFS) ፕሮግራም የስትሪንግ ኮሚቴ በሚዛን አማን ከተማ ውይይት አካሂዷል ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጂዮ ሳፒ እንደገለፁት ክልሉ ከተቋቋመ ጥቂት ዓመታት መሆኑን ጠቁመው ከቀድሞው ክልል የተረከባቸው በርካታ የመሠረተ ልማት ዕዳዎች መኖራቸውን ተናግረዋል ። የክልሉን ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የተመቻቸ ለማድረግ የመንገድ መሠረተ ልማቶችን ምቹ ሁኔታ መፍጠር የግድ በመሆኑ መንግስት አቅዶ ከሚሰራው ባሻገር…

Read More

የውስጠ ፓርቲ አንድነትን በማጠናከር የብልጽግና ፓርቲ ጉዞን እውን ለማድረግ አመራሩ እና አባሉ በቁርጠኝነት ሊሰራ እንደሚገባ ተገለፀ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የቴፒ ብዝሃ ማዕከል የክልል ሴክተር የብልጽግና ፓርቲ ህብረት የ2017 በጀት ዓመት 3ኛ ሩብ ዓመት የአባላት ኮንፈረንስ በቴፒ ከተማ አካሂዷል። በአባላት ኮንፈረንስ ላይ ንግግር ያደረጉት ቴፒ ብዝሃ ማዕከል የብልጽግና ፓርቲ ህብረት ሰብሳቢ አቶ ደምሴ ደንቦ የፓርቲውን አሰራሮች እና አደረጃጀቶችን በማጠናከር የውስጠ ፓርቲ አንድነትን በማጉላት ተግባራትን የመምራት…

Read More

የወጪ ንግድ ዘርፍ አፈጻጸምን በዓመቱ መጨረሻ 7 ቢሊየን ዶላር ለማድረስ እየተሰራ ነው፦ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)

የወጪ ንግድ ዘርፍ አፈጻጸም ባለፉት 9 ወራት ከተመዘገበው 5 ነጥብ 3 ቢሊየን ዶላር በዓመቱ መጨረሻ 7 ቢሊየን ዶላር ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈፃፀምና የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ አፈፃፀም የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል። ካሳሁን ጎፌ…

Read More

ባለፋት ዘጠኝ ወራት ወደ ውጭ ከተላከ የቡና ምርት ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበላ ያለፉት ዘጠኝ ወራት የቡና ንግድ አፈፃፀምን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ባለፋት ዘጠኝ ወራት ወደ ውጭ ከተላከ የቡና ምርት ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት 299 ሺህ 607 ቶን ቡና በመላክ ከእቅድ በላይ ማሳካት መቻሉንም ጠቅሰው፤…

Read More

የመንግሥት ተቋማት ለህዝቡ የሚሰጡት አግልግሎት ጥራትና ፍትሀዊ ተደራሽነትን ያረጋገጠ መሆን አለበት፦ ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

የመንግሥት ተቋማት ለህዝቡ የሚሰጡት አግልግሎት ጥራትና ፍትሀዊ ተደራሽነትን ያረጋገጠ መሆን እንዳለበት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ ገለጹ። የክልሉ ጤና ቢሮ የመንግሥት የጤና ተቋማት አግልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ ያተኮረ ክልላዊ ንቅናቄ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ በተገኙበት በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። በመንግሥትና መሪው የብልጽግና ፓርቲ በልዩ…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የቬይትናም ይፋዊ ጉብኝት

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሀኖይ ቬይትናም ይፋዊ ጉብኝት በማድረግ ላይ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በ2025 የፒ4ጂ ቬይትናም ጉባኤ ላይም ይሳተፋሉ። በቆይታቸው ከቬይትናም የፀሃይ ኃይል ማመንጫዎች በማምረት ወደ ውጭ የሚልከውን ቶዮ ሶላር የተባለውን ፋብሪካ ጎብኝተዋል። ድርጅቱ በቅርቡ በሀዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክ በመግባት በኢትዮጵያ ሥራ ጀምሯል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድርጅቱ ከፀሃይ ኃይል…

Read More

ቤላሩስ ከኢትዮጵያ ጋር በቴክኖሎጂ ዘርፍ በትብብር መስራት እንደምትፈልግ ገለጸች

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ከቤላሩስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማክሲም ሪዤንኮፍ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም ሁለቱ ሀገራት በቴክኖሎጂ ዘርፍ በትብብር መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡ በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት፥ ቤላሩስ በባለብዙ ወገን መድረኮች ላይ ለኢትዮጵያ ላደረገችው ድጋፍ በማመስገን ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል። ኢትዮጵያ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና በሌሎች ዘርፎች አበረታች ውጤት እያስመዘገበች መሆኑን ጠቁመው፥ ከአጋር ሀገራት…

Read More

ኢትዮጵያ እና ቤላሩስ የጋራ ተጠቃሚነታቸውን በሚያረጋግጡ መስኮች ላይ በትብብር እንደሚሰሩ ገለጹ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) የቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማክሲም ሪዜንኮቭን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ሚኒስትሮቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የቤላሩስ ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ሉካሼንኮ እ.አ.አ በኦክቶበር ወር 2024 በሩሲያ ካዛን ከተካሄደው የብሪክስ ጉባኤ ጎን ለጎን ያደረጉትን የሁለትዮሽ ውይይት አንስተዋል። ውይይቱ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር ወሳኝ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ጌዲዮን (ዶ/ር) ኢትዮጵያ…

Read More

በክልሉ የመንግሥት የልማት ሥራዎችን የሚያደናቅፉ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን በተቀናጀ መንገድ መፍታት ያስፈልጋል፦ርዕሰ መስተዳድር ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የአስተዳደር ዘርፍ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት ባለፉት የ9ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሸ ዋጌሾ በተገኙበት ተገምግሟል። በዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረኩ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በአስተዳደር ዘርፍ ተቋማት ታቅደው በጥንካሬ የተከናወኑ ተግባራት እንዲጠናከር፣ በክፍተት የታዩትን በመገምገም እና ቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ላይ ሀሳብ አስተያየት ተነስተው በጥልቀት ውይይት ተደርጓል።…

Read More

በክልሉ በካፒታል በጀት የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች በተገቢው ተጠናቅቆ የህዝብ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል:-የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ

የክልሉ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላት በክልሉ በሁሉም አከባቢዎች ባደረጉት የካፒታል ፕሮጀክቶች አፈፃፀም ምልከታ ዙሪያ የግብረ መልስ መድረክ በታርጫ ከተማ ተደርጓል። የክልሉ ቋሚ ኮሚቴ አባላት በክልል በሁሉም አከባቢዎች በካፕታል በጀት እየተሰሩ ያሉ ወደ 20 የሚጠጉ የጤና፣ የውሃ እንዲሁም የኮሌጆች የግንባታ ሂደት ያለበትን ደረጃ የመስክ ምልከታ አድርገዋል። የአስፈፃሚ ተቋማት በፅሁፍ የሚያቀርቡትን ሪፖርት በተግባር በማረጋገጥ ለፕሮጀክቶች አፈፃፀም…

Read More