የቤንች ሸኮ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ መካሄድ ጀምሯል።
በመድረኩ ላይ የዞኑን ወቅታዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች በመፈተሽ፣ የአመራሩን ቁመና የማጥራት ስራ ትኩረት እንደሚሰጠው ተገልጿል። በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ዋና አፈ ጉባኤ ክቡር አቶ ወንድሙ ኩርታ ዞኑ በክልል ደረጃ የተሻለ አፈፃፀም እያስመዘገበ ያለ ዞን መሆኑን ጠቅሰዋል። ይሁን እንጂ የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠልና ህዝባዊ አገልጋይነትን ለማረጋገጥ አመራሩን በሦስት ዋና…
