ኢትዮጵያ በዱባይ እየተካሄደ ባለው ዓለም አቀፍ የፖሊስ ጉባኤ ላይ እየተሳተፈች ነው
ኢትዮጵያ “ደህንነቱ ለተጠበቀ ነገ ዓለም አቀፍ የፖሊስ ኃይል ትብብር” በሚል መሪ ሀሳብ በዱባይ እየተካሄደ ባለው ዓለም አቀፍ የፖሊስ ጉባኤ ላይ እየተሳተፈች ነው። በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የተመራው ልዑክ በፈረንጆቹ ከመጋቢት 5 እስከ 7 ቀን 2024 በዱባይ እየተካሄደ ባለው ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያን ወክለው እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡ ልዑካን ቡድኑ በቦታው ሲደርስ በዱባይና ሰሜን ኤምሬቶች የኢፌዲሪ…
