Trendings

በ557 ሚሊዮን ብር በመገንባት ላይ የሚገኘው የጀሙ 2ኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ ያለበት ደረጃ ተጎበኘ

በምዕራብ ኦሞ ዞን በጀሙ ከተማ በትምህርት ሚኒስቴር በ557 ሚሊዮን ብር በጀት የሚገነባው አዳሪ ትምህርት ቤት ተጎብኝቷል ። በጉብኝቱ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ ጨምሮ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታምሩ ቦኒ ፤ የክልል፣ የዞንና የጀሙ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በቦታው ተገኝተው ጉብኝት አድርጓል። የትምህርት ቤቱ ግንባታ እስከ ሰኔ 2018…

Read More

በሚዛን አማን ከተማ የሰንበት ገበያ ተጠናክሮ ቀጥሏል፤ ለገበያው መሳካት ከ2.8 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጓል

​በሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር የኑሮ ውድነትን ለመቋቋም እና ህብረተሰቡን በተመጣጣኝ ዋጋ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመረው የሰንበት ገበያ፣ በሁለቱም ማዕከላት (ሚዛንና አማን) በልዩ ትኩረት ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ። ​የከተማ አስተዳደሩ የሰንበት ገበያን ዘላቂና ምቹ ለማድረግ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ እያፈሰሰ ይገኛል። ለዚህም ይረዳ ዘንድ በሚዛንና በአማን ለሚገኙ የገበያ ማዕከላት ከ2.8 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ግዙፍ የገበያ ድንኳኖች ግዥ…

Read More

ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ም/ቤቶች የ2018 የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ በዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-

ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ም/ቤቶች የ2018 የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ በዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡- የኢትዮጵያ የጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና በመደርጀት ላይ ይገኛል ፤ ይህ ስትራቴጂያዊ ምርጫም ኢትዮጵያን ከታዛቢነት ወደ አጀንዳ ተላሚነትና ተጽዕኖ ፈጣሪነት ለማሸጋገር አስችሏል፣ በድንበር ተሻጋሪ ሀብቶቿ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ስትቀበል፤ ከዚሁ ጎን ለጎን አስተማማኝ የባሕር በር የማግኘት መብቷን…

Read More

በመማር ማስተማር ሂደት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቅረፍ የትምህርት ስራን ውጤታማ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው፦ ዶ/ር ደስታ ገነሜ

በመማር ማስተማር ሂደት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመቅረፍ የትምህርት ስራን ውጤታማ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቤሮ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ደስታ ገለጹ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከዩኒሴፍ በመተባበር ተደጋግሞ መጠቀም የሚያስችል የንጽህና መጠበቂያ ቁስ ማምረትና መጠቀም ዙሪያ ለተማሪዎች የክህሎት ስልጠና በቦንጋ ከተማ እየሰጠ ይገኛል። በስልጠና መርሃ ግብር የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ ም/ኃላፊ ዶ/ር…

Read More
ምክትል ርዕሰ መስተዳድር

ቋሚ የሥራ ዕድል በመፍጠር የዜጎችን ህይወት በዘላቂነት ለማሻሻል ትኩረት መስጠት ይገባል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኢንተርፕራይዞችና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ የወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸምን ከባለድርሻ አካላት ጋር ገምግሟል። ቢሮው በሩብ ዓመቱ በወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ስራ ላይ በተሰሩ ተግባራትና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በቦንጋ ከተማ ገምግሟል። በክልሉ ስራ ፈላጊ ዜጎችን በየማህበራዊ መሠረት በመለየት የክህሎትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና…

Read More

የህዝቦች ትስስር የተጠናከረበት የሸኮ ብሔር ድንቅ ባህላዊ ዕሴት – ቲካሻ ቤንጊ

የበለፀገች የጋራ ሀገር ለመገንባት እና የህዝቦች አንድነትን ለማጠናከር ከነጠላ ትርክት በመላቀቅ አርበኝነትን የሚያጎሉ አሰባሳቢ ትርክቶችን ለትውልድ ማሳወቅ፣ ማስተማር እና ማስረጽ ወቅቱ የሚፈልገው የሀሳብ ልዕልና ነው። ህብረ ብሄራዊት በሆነችው ኢትዮጵያ ህብረብሄራዊ ወንድማማችነትን እና እህትማማችነትን የሚያጎሉ ፣ አብሮነትን፣ እና ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት የሚያስችሉ እንዲሁም ብሔራዊነትን የሚያጎለብቱ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል። የሸኮ የባህል አባቶች በብሔረሰቡ አዲስ ዓመት…

Read More

የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ በቅየሳ ዙሪያ ለካዳስተር ባለሙያዎች የክህሎት ስልጠና እየሰጠ ነው::

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ከኢፌዲሪ ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በካዳስተር ቅየሳ ዙሪያ ለዘርፉ ባለሙያዎች የክህሎት ስልጠና በቦንጋ ከተማ እየሰጠ ይገኛል። በስልጠናው የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊና የከተማ መሬት መረጃና ምዝገባ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ቤተልሔም ተሾመ በክልሉ በሁለተኛ ደረጃ እና ሶሰተኛ ደረጃ የመሬት መቆጣጠሪያ ነጥቦች ላይ ንባብ…

Read More

በዞኑ ሰፊው ወጣቶችን የሚያቅፍ የገጠር የወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት ተሰጥተው እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ ኮንታ ዞን በተያዘው በጀት ዓመት ሰፊ ወጣቶችን የሚያቅፍ የገጠር፣ የወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ ገለጸዋል። በዞኑ፣ አመያ ዙሪያ ወረዳ፣ በጊምባ አጋሬ ቀበሌ በቡና ልማት ኢንዱስትሪ የተሰማሩ ወጣቶች በበኩላቸው በዘርፉ ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በዞኑ የወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራን በመሠረታዊነት በመደገፍ ዘርፉን ለማሻገር…

Read More

የመንግስት ተቋማት ከመደበኛ ስራቸዉ ጎን ለጎን በሰብዓዊ እና ማህበራዊ አገልግሎት ላይ ትኩረት ሰጥተዉ እንዲሰሩ ጥሪ ቀረበ፦አቶ ጥላሁን ታደመ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በታርጫ ከተማ አስተዳደር 02 ቀበሌ አረንጓዴ መንደር ለአቅመ-ደካማ ሴት ያስገነባውን ቤት መርቀው አስረክበዋል። በርክብክቡ ወቅት የተገኙት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ጥላሁን ታደመ የመንግስት ተቋማት ከመደበኛ ስራቸዉ ጎን ለጎን በሰብዓዊ እና ማህበራዊ አገልግሎት ላይ ትኩረት ሰጥተዉ እንዲሰሩ ጥሪ አቀርበዋል። አክለውም የመንግስት ተቋማት ከመደበኛ ስራቸዉ ጎን…

Read More

የ4 ክልሎች የጋራ ሃብት የሆኑ የልማት ድርጅቶች አፈጻጸም ግምገማ እየተካሄደ ነው

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች፣ የደቡብ ኢትዮጵያ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና የሲዳማ ክልሎች የጋራ ሃብት የሆኑ የመንግስት የልማት ድርጅቶች አፈጻጸምና አጠቃላይ ተቋማቱ ያሉበትን ደረጃ የሚገመግም የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡ በቀድሞው የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል መንግስት ተቋቁመው የነበሩ እና አራቱም ክልሎች ሲደራጁ የጋራ ሃብት ሆነው እንዲቀጥሉ የተወሰኑ የመንግስት የልማት ድርጅቶች አፈጻጸም ነው እየተገመገመ የሚገኘው፡፡ የደቡብ…

Read More