Trendings

በጋምቤላ ክልል ከወዳደቁ ፕላስቲኮች ነዳጅ ማምረት የቻለው ግለሰብ

በጋምቤላ ክልል አኙዋ ዞን ጎግ ወረዳ የሚኖረው አቶ ኡጁሉ ኡሞድ የወዳደቁ ፕላስቲክ እቃዎችን እና ፌስታሎችን በመሰብሰብ የቤንዚን እና የናፍታ ነዳጅ ማምረት ችሏል። የወዳደቁ ፕላስቲኮችን እና ፌስታሎችን ሲሰበስብ ሰዎች እንደ እብድ ይቆጥሩት እንደነበር የገለጸው አቶ ኡጁሉ፤ የወዳደቁ የፕላስቲክ እቃዎችና ፌስታሎችን በመሰብሰብ የቤንዚንና ናፍታ ነዳጅ በመስራት ውጤታማ መሆኑን ገልጿል። በአሁኑ ሰዓት የነዳጅ ምርቱ በጀነሬተር እና በሞተር ሳይክል…

Read More

በካፋ ዞን የተለያዩ ከተማ አስተዳደሮች “የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ የኢትዮጵያን ማንሰራራይ እውን እናደርጋለን!” በሚል መሪ ሃሳብ ከነዋሪዎች ጋር ውይይት እየተካሄደ ነው።

መድረኮቹ በሁሉም ዘርፎች የተመዘገበዉን ለዉጥ በማስቀጠል የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቅነት በመፍታት የህዝቡን ተጠቃሚነት በሁሉም ዘርፍ ማረጋገጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ያጠነጠነ ነው። የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ውይይቱን የመሩት የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ መጠነ ሰፊ ተግባር መከናወኑን ገልጾ በዚህም ለህዝብ ድምፅ ትኩረት በመስጠት ማዘጋጃ ቤት ላይ ያደረገው የሪፎርም ስራና 13…

Read More

ኢትዮጵያ ያዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ ተከፈተ

ኢትዮጵያ ያዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ ተከፍቷል። ይህንን ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ፣ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ አንዱዓለም እና የመሀመድ ቢን ዛይድ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ዶክተር ከሊፋ ሙባረክ ከፍተውታል። በኮንፈረንሱ ላይ ከ16 ሀገራት የተውጣጡ የሃይማኖት አባቶችና የተቋማት መሪዎች እየተሳተፉ ነው። ኮንፈረንሱ በልዩ ልዩ መርሀ ግብሮች እስከ ነገ…

Read More

የስራ እድል ፈጠራን በተመለከተ

በተያዘው በጀት ዓመት ለ4 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር እቅድ ተይዟል፡፡ከዚህም ውስጥ 700 ሺህ ለሚሆኑት የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ለመፍጠር እቅድ የተያዘ ሲሆን፤ ባለፉት ሶስት ወራት ለሰለጠኑ ለ100 ሺህ ዜጎች በውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ተፈጥሯል፡፡ ኮዲንግ እና የመረጃ ትንተናን ጨምሮ በርቀት ስራዎች ደግሞ ለ26 ሺህ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሯል፡፡

Read More

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዓድዋ ድልን አስመልክቶ ሀገር አቀፍ ውይይት እያካሄደ ነው::

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ‘‘ዓድዋ የህብረ ብሄራዊነት ድምቀት የአንድነት ውጤት’’ በሚል ሀገር አቀፍ ውይይት እያካሄደ ነው። ውይይቱ 128ኛውን የዓድዋ ድል ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ ሲሆን ÷ የተለያዩ ፅሁፎችም ቀርበዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት ÷ ዓድዋ የዛሬ 128 ዓመት የተገኘ ድል ብቻ ሳይሆን ለዛሬው ትውልድና ለወደፊቱ ትውልድ ትምህርት የሚሰጥ ነው። የነገዋ…

Read More

የበጎ ተግባር ህዝብ ለህዝብ ትስስርንና እህትማማችነትን ከማጠናከር አኳያ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ

ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶች ክንፍ አደረጃጀት የተውጣጡ ወሰን ተሻጋሪ በጎ አድራጊ ልዑክ በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ የወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ አገልግሎት አከናውነዋል። የልዑክ ቡድኑ አባላት በሆሳዕና ከተማ ለአቅመ ደካማ ቤት ግንባታ የሚውል ቁሳቅስ፣ለህጻናት የትምህርት ቁሳቁስና የንጽህና መጠበቂያ አስረክበው የሌማት ቱሩፋት ልማትም ጎብኝተዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ኤልሳቤጥ…

Read More

ከነባሩ የሃሳብ አጥር በመውጣት የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በጋራ እንስራ:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከነባሩ የሃሳብ አጥር በመውጣት የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በጋራ እንስራ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን አስመልክተው “የምሁራን ሚና ለሀገራዊ ብልጽግና” በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ አቅርበዋል፡፡ በጽሑፋቸውም ለሀገር እድገት የግል ዘርፍን ጉድለት የሚሞላ፣ ሃሳብ የሚገዛ፣ ጠንካራ የመምራትና የመመልከት አቅም ያለው መንግሥት አስፈላጊ መሆኑን አብራርተዋል።…

Read More

የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ቀረበ

የፌዴራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ቀርቧል፡፡ የረቂቅ በጀቱን መግለጫ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አቅርበው ውይይት እየተካሄደበት ነው። ከ2018 ረቂቅ በጀት 1.2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ፣ 415 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ፣ 315 ቢሊዮን ብር ለክልል መንግስታት ድጋፍ እንዲሁም 14 ቢሊዮን ብር ለክልሎች የዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ድጋፍ…

Read More

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ላይ የሚቀመጡ ተማሪዎች ምዝገባ እየተካሄደ ነው::

በ2016 ዓ.ም በሚሰጠው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ላይ የሚቀመጡ ተማሪዎች ምዝገባ ከየካቲት 3 ቀን ጀምሮ እየተካሄደ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል። አገልግሎቱ የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የምዝገባ ሂደትን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ዘንድሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ማከናወን የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት በመደረግ ላይ መሆኑን የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ…

Read More