ኮርፖሬሽኑ አርሶ አደሩ የግብርና ግብዓት አቅርቦት እንዲያገኝ ለማስቻል ቅርንጫፍ ማዕከላትን እያጠናከረና እያስፋፋ ነው
የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን አርሶ አደሩ የግብርና ግበዓቶችን በአቅራቢያው እንዲያገኝ ለማስቻል ቅርንጫፍ ማዕከላትን እያጠናከረና እያስፋፋ መሆኑን ገለጸ። የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ክፍሌ ወልደማሪያም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን በኮርፖሬሽኑ ቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓት ሜካናይዜሽን ማዕከል ግንባታና የበቆሎ ዘር ብዜት ማሳን በመስክ ተመልክተዋል። በዚህ ወቅት አቶ ክፍሌ እንዳሉት፤ ኮርፖሬሽኑ ግብርናውን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ…
