Trendings

ለሸክ ኖኖ ቋንቋ ዘላቂ ዕድገትና ጥበቃ ማድረግ የአካባቢውን ባህልና የማንነት መሠረት ከመጠበቅ አንፃር ወሳኝ ጉዳይ ነው፦አቶ አልማው ዘውዴ

የሸካቾ ብሔረሰብ የባህልና ቋንቋ ሲምፖዚየም በሸካቾ ባህል፣ቋንቋና ሀገር በቀል ዕውቀት ላይ ያተኮረ ጥናታዊ ፅሁፍ ቀርቦ ሀሳብ አስተያየት ተሰጥቶበት ተጠናቋል። የሸክ ኖኖ ቋንቋን ዘላቂ ዕድገትና ጥበቃ የማረጋገጡ ተግባር የሁሉንም አካላት የተቀናጀ ጥረት የሚጠይቅ መሆኑ ተመላክቷል። የሀገር በቀል ዕውቀት የአንድ ማኅበረሰብ ቋንቋ፣ ባህል፣ ታሪክ መሠረት በመሆኑ ዕውቀቱን መጠበቅና ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባም ተገልጿል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል…

Read More

የሻይ ልማት ከኢኮኖሚ ጠቃሜታው ባሻገር የአካባቢውን ስህነ ምዳር በመጠበቅ ረገድም ሚናው የጎላ ነው፦ አቶ ማስረሻ በላቸው

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን በሻይ አመራረት ዘዴ ላይ ለዞን፣ ለወረዳና ለቀበሌ ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና በቦንጋ ከተማ እየሰጠ ይገኛል፡፡ የስልጠናውን መድረክ ያስጀመሩት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው የሻይ ልማት በክልሉ የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን በሚደረገው ሂደት ውስጥ ለአካባቢያችን ከፍተኛ ገቢ በማስገኘት አይናተኛ ሚና እንዳለው ተናግረዋል፡፡…

Read More

advd

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በ6ኛው ዙር ስልጠና የሚወስድ 50 ሰልጣኝ ዲፕሎማቶች ስልጠና አስጀምሯል። በስልጠና ማስጀመሪያው የሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ንጉስ ታደሰ እንዳሉት ፣ ዩንቨርስቲው በዲፕሎማሲ ዘርፍ በቂ ስልጠና መስጠት የሚያስችል አቅምና ልምድ አለው። ዩኒቨርስቲው ዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል ከፍቶ ተማሪዎችን እያሰለጠነ ይገኛል ብለዋል። ሰልጣኝ ዲፕሎማቶችም ዓለም አቀፍ ነባራዊ ሁኔታን መረዳት የሚያስችል እውቀት ይዘው…

Read More

የኢትዮጵያ የባህር በር ማግኘት የዓድዋ ሰማዕታት ካወረሱን የሉዓላዊነት አደራ የማይነጠል ነው – ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ

የኢትዮጵያ ዘላቂና አስተማማኝ የባህር በር ማግኘት የዓድዋ ሰማዕታት ካወረሱን የታሪክና የሉዓላዊነት አደራ የማይነጠል መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ገለጹ። ፕሬዚዳንቱ ይህን ያሉት 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል መሪ ሀሳብ በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተከበረ በሚገኘው መድረክ ላይ ነው። የዓድዋ ድል ለአፍሪካና ለመላው ጥቁር ህዝብ የነፃነት ጎህ የፈነጠቀና ሰብዓዊ ክብርን ያጎናጸፈ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የዘመን መለወጫን በማስመልከት ለ745 ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የዘመን መለወጫን በማስመልከት ለ745 ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት፣ አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ በክልሉ በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ የሕግ ፍርዳቸውን ሲፈጽሙ የቆዩ 745 ታራሚዎችን በይቅርታ እንዲፈቱ መወሰኑን አስታወቀ። ይቅርታ ከተደረገላቸው ታራሚዎች መካከል 720ዎቹ ወንዶች ሲሆኑ 25ቱ ደግሞ ሴቶች ናቸው። ውሳኔው የክልሉ የይቅርታ ቦርድ፣ ታራሚዎቹ ካቀረቡት…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዛሬ ለምክር ቤቱ ማብራሪያ እና ምላሽ ይሰጣሉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዛሬ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመገኘት ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በፌዴራል መንግስት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የአፈፃፀም ሪፖርትን መነሻ በማድረግ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ እና ማብራሪያ እንደሚሰጡ ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

Read More

አየር መንገዱ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን ኤ350-1000 የተሰኘ አውሮፕላን በቅርቡ እንደሚረከብ አስታወቀ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውና ”Ethiopia land of origins” በሚል መጠሪያ የተሰየመውን ኤ350-1000 የመንገደኞች አውሮፕላን በተያዘው ጥቅምት ወር ከኤርባስ ኩባንያ እንደሚረከብ አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው እንደገለጹት፣ አየር መንገዱ በአፍሪካ የአቪዬሽን መስክ ያለውን የቀዳሚነት ድርሻውን ለማስቀጠል በየጊዜው አዳዲስ አውሮፕላኖችን በማስመጣት እንዲሁም ዓለም አቀፍ መዳረሻዎቹን በማስፋት ላይ ይገኛል። በዚህም…

Read More

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

የኢትዮጰያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አለምአቀፍ ትስስር ዘላቂ ለማድረግ ወደ 25 ሚሊዮን የሚጠጉ መንገደኞችን በአመት የማስተናገድ አቅሙ ላይ ከደረሰው ከአዲስ አበባ ቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋ ጣቢያ እየለማ ይገኛል። ይኽ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግምባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ አላማን ያነገበ ነው።…

Read More

“ባለፉት ሶስት ወራት ከ20 የማያንሱ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች በኢትዮጵያ ተካሂደዋል”

ባለፉት ሶስት ወራት ከ20 የማያንሱ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች ተካሂደዋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስተርር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ባለፈው ዓመት ዓመቱን ሙሉ 20 ዓለም አቀፍ ኮንፈረሶችን አላካሄድንም፤ ዘንድሮ በሶስት ወር ብቻ 20 የሚደርሱ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶችን አካሂደናል ብለዋል፡፡ በቀጣይም በርካታ ዓለም ዓቀፍ ኮንፈረንሶች በኢትዮጵያ ይካሔዳሉ ሲሉ አመላክተዋል፡፡ የኮሪደር ልማት እና በኢትዮጵያ የተፈጠረው አውድ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ኮንፈረንሶችን…

Read More

በዞኑ ታሪካዊ ዋሻዎችንና የተፈጥሮ መስህቦችን በማልማት ለወጣቶች የስራ ዕድል ለመፍጠር እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ሸካ ዞን ገለጸ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የምትገኘውና በአብዛኛው ጥቅጥቅ ባሉ ደኖች የተሸፈነችው ሸካ ዞን፣ በውስጧ ያቀፈቻቸውን ታሪካዊና ተፈጥሯዊ የቱሪስት መዳረሻዎችን የመለየትና የማልማት ስራ መጀመሩን የዞኑ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው የቱሪዝም ፕሮሞሽንና ግብይት ቡድን መሪ አቶ ብርሃኑ አያሾ እንደገለጹት፣ በዞኑ ወረዳዎችና ከተሞች በጥናት ላይ የተመሰረተ የመስህብ ስፍራዎችን የመለየት ስራ ተከናውኗል። ይህ ጥረትም ዞኑ ከያዘው የተፈጥሮ…

Read More