ኮሚሽኑና የሐይማኖት ተቋማት በጋራ ለመሥራት ግብረ-ኃይል አዋቀሩ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እና የሐይማኖት ተቋማት በቀጣይ በጋራ በሚሠሯቸው ተግባራት ላይ ግብረ-ኃይል በማቋቋም በትብብር ለመስራት ተስማሙ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሐይማኖት ተቋማትን ሚና እና ተሳትፎ በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ለማጎልበት ያለመ ውይይት በአዲስ አበባ ከተማ አካሂዷል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ የሐይማኖት ተቋማት ጉባዔ አባላት እና በጉባዔው በአባልነት ያልተመዘገቡ የሐይማኖት ተቋማት መሳተፋቸውን የኮሚሽኑ መረጃ አመላክቷል፡፡ የኮሚሽኑ ዋና…
