Trendings

ኮሚሽኑና የሐይማኖት ተቋማት በጋራ ለመሥራት ግብረ-ኃይል አዋቀሩ

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እና የሐይማኖት ተቋማት በቀጣይ በጋራ በሚሠሯቸው ተግባራት ላይ ግብረ-ኃይል በማቋቋም በትብብር ለመስራት ተስማሙ፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሐይማኖት ተቋማትን ሚና እና ተሳትፎ በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ለማጎልበት ያለመ ውይይት በአዲስ አበባ ከተማ አካሂዷል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ የሐይማኖት ተቋማት ጉባዔ አባላት እና በጉባዔው በአባልነት ያልተመዘገቡ የሐይማኖት ተቋማት መሳተፋቸውን የኮሚሽኑ መረጃ አመላክቷል፡፡ የኮሚሽኑ ዋና…

Read More

የዘንድሮው የማሽቃሮ በዓል በታላላቅ ሀገራዊና ታሪካዊ ክስተቶች ታጅቦ በድርብ ደስታ ይከበራል – አቶ ፍቅሬ አማን

የህዳሴው ግድብ ምርቃትና የካፋው ንጉስ የታቶ ጋኪ ሻሬቾ ዘውድ መመለስ ለበዓሉ ልዩ ድምቀት ሰጥተውታል ስሉ አቶ ፍቅሬ አማን ገልጸዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን፣ ለካፌቾ ብሔር የዘመን መለወጫ ‘ማሽቃሮ’ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ኃላፊው በመልዕክታቸው ፣ የዘንድሮው በዓል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በታላቅ ስኬት መመረቅና የካፋ…

Read More

የኢትዮጵያ የሚዲያ ልህቀት ማዕከል ስራ ጀመረ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን የመገናኛ ብዙሃንን አቅም ለማሳደግ በሚል ያቋቋመው የሚዲያ ልህቀት ማዕከል በይፋ ስራ ጀምሯል። በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ እንዳሉት፤ በሰላም፣ በመልካም አስተዳደር ዘርፍም ሆነ በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ወቅታዊና ትክክኛ መረጃ በማቅረብ መገናኛ ብዙሃን ሚናቸው የጎላ ነው። ሚዲያዎች ለማህበረሰብ እድገት የራሳቸውን ሚና በመጫወት የኢትዮጵያን እድገት ለማረጋገጥ…

Read More

የኢትዮጵያ ፈተናዎችን ሁሉ የተሻገረ ያለመበገር ፅናት የምጣኔ ሀብት መረጋጋትንና ምርታማነትን ባስቀደሙት በመዋቅራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስራዎቿ ማሳያነት ይገለጣል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)::

የኢትዮጵያ በፈተናዎች ሁሉ የተሻገረ ያለመበገር ፅናት የምጣኔ ሀብት መረጋጋትንና ምርታማነትን ባስቀደሙት በመዋቅራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስራዎቿ ማሳያነት ይገለጣል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናገሩ። በብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን በሚመራው ስራ ምክክር እና እርቅ የሰላም ፍላጎታችን እና ተምኔታችን ማጠንጠኛ ናቸው ሲሉም ገልጸዋል። ትምህርትን ተደራሽ በማድረግ ብሎም ወጣቶችን በማብቃት ኢትዮጵያ ሁለት ሚሊዮን አዳዲስ ስራዎችን ለመፍጠር እንዳለመችም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና የኦሮምያ ክልል ርዕሰመስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ጋር በአምቦ ወረዳ በነበራቸው ጉብኝት የኬኛ ቤቭሬጅ ፋብሪካን ተመልክተዋል። ፋብሪካው በመጪዎቹ ሶስት ሳምንታት ውስጥ ወደሥራ የሚገባ ሲሆን 3 ሚሊዮን ሄክቶሊትር የማምረት አቅምም አለው።

የአስተዳደር ሥራን ወደ ሕዝብ ለማቅረብ የቀበሌዎች መጠናከር ወሳኝ ነው። የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በየአካባቢው ለሕዝብ ቅርብ የሆነ አስተዳደር ለመፍጠር (power devolution) ጥረት እያደረገ ነው። ከዚህ አንጻር በአምቦ ወረዳ የአንድ ቀበሌ እንቅስቃሴ በጉብኝት ወቅት ታይቷል። በዚህ ቀበሌን የማብቃት ተግባር በክልሉ 7342 ቀበሌዎች ተደራጅተዋል። 50,000 የሰው ኃይል ተመድቦላቸዋል። ከዚህ ቀደም በወረዳዎች ተማክለው የነበሩ ሞያዊና አስተዳደራዊ አገልግሎቶች በቀበሌ ደረጃ…

Read More

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በርካታ የውጭ ኢንቨስትመንቶችን እየሳበ ነው

የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በርካታ የውጭ ኢንቨስትመንቶችን እየሳበ ነው አሉ፡፡ በኢትዮጵያ እና ቤልጂየም የኢንቨስትመንት ዘርፍ ትብብር ላይ ያተኮረ የቢዝነስ መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡ አቶ አህመድ ሺዴ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በርካታ የውጭ ኢንቨስትመንቶችን እየሳበ ነው ብለዋል፡፡ 10 የሚጠጉ የቤልጂየም ኩባንያዎች የተሳተፉበት የልምድ ልውውጥ መድረክ የዚህ ፍላጎት አካል መሆኑን…

Read More

የፌዴሬሽን ምክር ቤት እና የፍትሕ ሚኒስቴር በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ አደረጉ

የፌዴሬሽን ምክር ቤት በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ የተጎዱ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም የሚውል የ3 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል። በተመሳሳይ የፍትሕ ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማቱ ጋር በመሆን ተጎጂዎችን ለማቋቋም የሚውል የ3 ሚሊዮን ብር የገንዘብ እና የ100 ኩንታል ዱቄት ድጋፍ አድርጓል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር አርባ ምንጭ ከተማ በመገኘት ድጋፍን ባስረከቡበት ወቅት፣ የሰላም ተምሳሌት…

Read More

የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ አጀንዳዎችን ከመፈጸም ጎን ለጎን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል፦አቶ ፍቅሬ አማን

በብልፅግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን የክልሉን የዘጠኝ ወራት የፓርቲ የሥራ አፈጻጸም እና 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ሥራዎች አስመልክቶ ለሚዲያዎች መግለጫ ሰጥተዋል። ኃላፊው በመግለጫቸው፤ በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት በፓርቲና መንግሥት የተመሩ የንቅናቄ አጀንዳዎች በተሳካ ሁኔታ መፈጸማቸውን ገልጸዋል። በፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ለአመራሮችና ለአባላት በየጊዜው የሚሰጡ ስልጠናዎች የአመለካከትና…

Read More

ርዕሰ መስተዳደሩ ሪፖርታቸዉን ማቅረብ እንደቀጠሉ ነዉ

1. የማህበራዊ ልማት ሥራዎች አፈፃፀምን በሚመለከት ➣ ህብረሰቡን በማስተባበር በብር 65,361,160 ብር በማሰባሰብ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተዘጋጁ የመማሪያ ማሰተማሪያ መጽሃፍትን በማሳተም ተደራሽ ማድረግ ተችሏል፡፡ ➣ ከ1ኛ-6ኛ እንግሊዘኛ መፅሀፍት በቁጥር 104,000 በክልሉ መንግስት በ21 ሚሊዮን ብር በማሳተም ወደ ዞኖች እና ት/ቤቶች ተሰራጭቶ ለመማር ማስተማር ስራ እንዲውሉ ተደርጓል፡፡ ➣ በትምህርት ለትዉልድ ንቅናቄ ስራ 414,704,720 ብር በመሰብሰብ 551…

Read More

ለፕሮግራሞች ማስፈጸሚያ በሚመደቡ ሀብቶች ውጤታማ ስራዎችን በማከናወን ተደማሪ ሀብት ለማግኘት ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተገለጸ

ክልላዊ የልማት ክፍተቶችን ለመቅረፍ መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች የሚመጡ ሀብቶችን ከዓለም ባንክ ጋር በተገባው ስምምነት መሰረት በተገቢው ስራ ላይ ማዋል እንደሚጠበቅም ተገልጿል ፡፡ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፋይናንስ ቢሮ የካልም ፕሮጀክት የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በቦንጋ ከተማ ተደርጓል ፡፡ በአፈጻጸም ግምገማው የተገኙት በክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ምክትል ኃላፊና የመንግስታት ትብብር ሲቪክ ማህበራት ዘርፍ ኃላፊ…

Read More