የሸካ ዞን የብልፅግና ፓርቲ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ በቴፒ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።
መድረኩ ከፓርቲው እሳቤና መርሆዎች ተነስቶ ተቋማት የተጣለባቸውን የህዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በአመራር መሪነት የተከናወኑ ተግባራትን በዝርዝር የሚገመግም መሆኑ ተገልጿል። የግምገማ መድረኩን እየመሩ የሚገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ ዓለሙ እንደገለጹት የመድረኩ ዋና ዓላማ የፓርቲውን ጠንካራ ጎኖች በማስቀጠል እና የታዩ ክፍተቶችን በግልጽ በመወያየት የአመራሩን የመፈጸም አቅም ማሳደግ መሆኑን ገልጸዋል። የአመራር…
