ኢትዮጵያ በዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኤጄንሲ ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች ነው::
14ኛው ዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኤጄንሲ ጉባዔ በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች አቡ ዳቢ በዛሬው ዕለት ተጀምሯል፡፡ በጉባዔው የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) እና በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች የኢትዮጵያ አምባሳደር ዑመር ሁሴን (ዶ/ር) ኢትዮጵያን በመወከል ተሳትፈዋል፡፡ በጉባኤው ከታዳሽ ኃይል እና የአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዘ በርካታ ሪፖርቶች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች የኢትዮጵያ ኤምባሲ…
