Trendings

የፕሮግራም በጀት አሰራር ስርዓቱን በየተቋማት ተግባራዊ በማድረግ ስራዎችን በውጤት ለመለካት እና ተጠያቂነትን ለማስፈን እንዲቻል በልዩ ትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፋይናንስ ቢሮ በፕሮግራም በጀት አሰራርና አተገባበር ዙሪያ በክልሉ በሚገኙ ለዘርፉ አመራሮች የተዘጋጀዉ ስልጠና በሚዛን አማን ከተማ እየተሰጠ ይገኛል። የስልጠናው ዓላማ የፕሮግራም በጀት አሰራርና አተገባበር፣ ክትትልና ሪፖርትን ለመለካት የሚያስችሉ የአሰራር ስርዓት ላይ የተሻለ ግንዛቤ ለመፍጠር ነው ተብሏል። በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ከበደ ከዚህ በፊት የነበሩ…

Read More

የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተቋማት የመረጃ ሥርዓት የዘመነ የህብረተሰቡን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ መሆን ይገባዋል፦ አቶ ታከለ ታምሩ።

በካፋ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት አመቻችነት በዞኑ የሚገኙ የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ተቋማት አመራሮችና ባለሙያዎች የመረጃ ሥርዓት ከማዘመን አኳያ በሚታዩ ተግዳሮቶችና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የጋራ ውይይትና ምክክር መድረክ አካሂዷል ፡፡ የካፋ ዞን የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ታከለ ታምሩ በመክፈቻ ንግግራቸው የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ተቋማት የመረጃ ሥርዓት የዘመነ፣ ችግር ፈቺና የህብረተሰቡን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆን ይገባቸዋል…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል እንደ ሀገር ከቡና ኤክሰፖርት ላደረገው ከፍተኛ አስተዋጽኦ እውቅና ተቸረው።

ክልልሉ እንደ ሀገር እየተጠናቀቀ ባለው የፈረንጆቹ አመት ለተገኘው 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር ገቢ ከፍተኛ አስተዋፅኦ በማበርከቱ ከኢፌዴሪ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ እጅ የዋንጫ ተሸላሚ ሁኗል።

Read More

“በሁሉም አካባቢ የሚኖረውን ህዝባችንን ፈተናዎች እና ፍላጎቶች ማዳመጥ ቀዳሚ ተግባራችን ነው”፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)::

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “በሁሉም አካባቢ የሚኖረውን ህዝባችንን ፈተናዎች እና ፍላጎቶች ማዳመጥ ቀዳሚ ተግባራችን ነው” ሲሉ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ ፤ከደቡብ፣ ደቡብ ምዕራብ፣ ሲዳማ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ከተወጣጡ ተወካዮች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ጠቁመዋል። በውይይቱም ተወካዮች በልማት ጉዳዮች ላይ አስተያየቶቻቸውን እና ጥያቄዎቻቸውን ማቅረባቸው የተገለጸ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጋራ ግብ ላይ…

Read More

በክልላችን የሴቶችን ተሳትፎ፣ ተጠቃሚነትና አበርክቶ ጎልቶ እንዲወጣ ሰፊ ስራዎች እየተሰራ ነው፡፡ አቶ ፍቅሬ አማን

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በቦንጋ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ በሁለተኛው መደበኛ ጉባኤ የተወሰኑ የውሳኔ አቅጣጫዎች ላይ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ህዝባዊ የውይይት መድረክ መካሄድ ተጀምሯል። በመድረኩ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን የፓርቲው ብልጽግና ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ከቃል እስከ ባህል በሚል መሪ ቃል መካሄዱን ጠቅሰው በዚህም…

Read More

ባለፉት ስድስት ወራት ያገኘነዉን ዉጤት አስጠብቀን በቀጣይ የተሻለ ለማስመዝገብ እንሰራለን:።ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በሰጡት ማጠቃለያ ምላሽ የምክርቤት አባላት ያነሱት ጥያቄዎች ከአዲጊ ፍላጎት የመነጨ መሆኑን በመግለጽ ተገቢነት ያለው ነው ብለዋል። ከቀድሞ ደቡብ ክልል ይዘናቸው የመጡ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ አለመጠናቀቃቸው ክልሉ ይዞት የመጣው የ5 ቢሊየን ብር ዕዳ የመመለስ ሁኔታ መኖሩን አብራርተዋል ። ከ2014 ጀምሮ እስከ 2015 ከነበረው 5 ቢሊዮን…

Read More

ኤክስፖርትን በተመለከተ

እቅድ አሳካክታ የማታውቅ ሀገር በዚህ አመት 5.1 ቢሊዮን ዶላር ኤክስፖርት ለማድረግ አቅዳ ከ8.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ያሳካች ሲሆን ከአቅድ ነው 3 ቢሊዮን ገደማ ጭማሪ ማግኘት የቻለች ሲሆን ከአምናው ከእጥፍ በላይ አሳክታለች፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አቢይ አህመድ

Read More

የብርቱካን ተመስገን ሕጋዊ የጋብቻ ውል

“ባለቤት አለኝ፤ አሁን እንዴት ነው ከባለቤቴ ጋር ሰላም የምናገኘው መተማመንስ የሚኖረን?” – ብርቱካን ተመስገን ሀሰተኛ ድራማ የተሠራባት ብርቱካን ተመስገን ቤተሰቦቻቸው ጋር ሄደው በአካባቢው ባህል መሰረት ትዳር እንደመሰረተች ራሷም ባለቤቷም ምሥክርነት ሰጥተዋል። በጋብቻዋም የሁለት ዓመት ልጅ እንዳፈራች እና በመልካም ሁኔታ ስትኖር እንደነበር ጎረቤቶቿን ጨምሮ ሁሉም ምሥክርነት ሰጥተዋል። ብርቱካን ከመዓዛ መሐመድ ጋር በስልክ ባደረገችው ንግግር ያስጨነቃት እንዴት…

Read More

የአቅም ደካሞች ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ ፕሮግራም በክልሉ ከሚከናወኑ ሰው ተኮር አገልግሎት አንዱ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ

የክልሉ ትምህርት ቢሮ አመራሮችና ተጠሪ ተቋማት በጋራ በመሆን በቦንጋ ከተማ 180 ሺህ በሚሆን የገንዘብ ወጪ የሚሰራ የአቅም ደካሞች ቤት ግንባታ ስራ አስጀምሯል፡፡ ቤት ግንባታ ፕሮግራሙን ያስጀመሩት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ የ2016 በጀት ዓመት የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በጎነት ለኢትዮጵያ…

Read More