Trendings

Getenesh Gebeyehu

በክልሉ በበጋ መስኖ ልማት በአንደኛ እና ሁለተኛ ዙር ከ95 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ በተለያዬ ሰብል ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ ከምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም /FSRP/ ጋር በመተባበር የ2017 ዓ.ም የበጋ መስኖ ልማት ላይ ለዞንና ወረዳ ባለሙያዎች የክህሎት ስልጠና በሚዛን አማን ከተማ እየሰጠ ይገኛል። ስልጠናው የበጋ መስኖ ሰብሎች አመራረት፣የመስኖ ውሃ አጠቃቀም እንዲሁም በGPS እና GIS አጠቃቀም የመረጃ አመዘጋገብ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የእርሻና…

Read More

የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድን አገልግሎት ለህ/ሰቡ የጤና አገልግሎት በፍትሀዊነት ተደራሽ ለማድረግ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ።

የክልሉ የህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን (ማአጤመ) ቦርድ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን የመዋጮ ክፍያ ምደባ ለማሻሻል በቀረበው መመሪያ አተገባበር ላይ ውይይት በታርጫ ከተማ አድርጓል። የቦርዱ ሰብሳቢ እና በክልሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ የማህበረሰብ አቀፍ መድን አገልግሎት ለህብረሰቡ የጤና አገልግሎት በፍትሀዊነት ተደራሽ ለማድረግ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ…

Read More

ግልጽና አሳታፊ የግዥ ስርዓትን በማስፈን ለግዥ የሚመደበው የመንግስት በጀት ለታለመለት ዓላማ ማዋል እንደሚገባ ተጠቆመ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ፋይናንስ ቢሮ በመንግሥት ግዥ ንብረት ባለስልጣን ለወረዳ የግዥ ባለሙያዎች በካልም ፕሮግራም በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በሚዛን አማን ከተማ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። በስልጠናው የክልሉ ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን የመንግስት ግዥና ንብረት ኦዲትና ክትትል ዳይሬክተር አቶ ታምራት ወርቁ ስልጠናው ግልጽና አሳታፊ የግዥ ስርዓትን በማስፈን ለግዥ የሚመደበው ውስን የመንግስት በጀት ለታለመለት ዓላማ ለማዋል…

Read More

የገንዘብ ሚኒስቴር እና የእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ በጋራ ለመስራት መግባባት ላይ ደረሱ

የገንዘብ ሚኒስቴር እና የእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ በጋራ ለመስራት መግባባት ላይ ደርሰዋል፡፡ የገንዘብ ማኒስትሩ አህመድ ሺዴ ከባንኩ ፕሬዚዳንት ጂን ሊኩውን ጋር ባደረጉት ውይይት፤ በጋራ መስራት በሚቻልባቸው የትብብር መስኮች ላይ መክረዋል። እንደ ሀገር እየተሰራበት ባለው የረጅም ጊዜ የእድገት ፕሮግራም፣ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርምና ሌሎችንም ተግባራት ኢትዮጵያ እያከናወነች መሆኑን ለባንኩ አመራሮች አስረድተናል ሲሉ አቶ አህመድ ተናግረዋል።…

Read More

የአውሮፓ ሕብረት የተፈጥሮ ሀብት ላይ ጉዳት እየደረሰ የሚመረቱ ምርቶችን በተመለከተ ባወጣው ህግ ላይ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቦንጋ ከተማ ውይይት ተደረገ

የውይይት መድረኩን ያዘጋጁት Consortium for Climate Change – Ethiopia እና NABU Ethiopia የተሰኙ ግብረ-ሠናይ ድርጅቶች በመተባበር ነው። በህጉ አተገባበር እና ተግዳሮቶች እንዲሁም ከአካባቢያዊ ሁኔታዎች አንፃር ግንዛቤ መፍጠር የመድረኩ ዓላማ ነው። የNABU ኢትዮጵያ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አስተባባሪ አቶ አሳየ ዓለማየሁ በመድረኩ እንደተናገሩት ፤ ውይይቱ ባለድርሻ አካላት ይህንን ህግ ባከበረ መንገድ ማምረት እንዲችሉና ሃላፊነታቸውን በአግባቡ…

Read More

gh

የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎችም የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ አመራር አባላት የባህር ዳር ከተማን የልማት እንቅስቃሴዎችን እየተመለከቱ ነው። በጉብኝቱ የብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ ሰማ ጥሩነህ (ዶ/ር)፣የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ መለስ አለሙ፣የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማውና ሌሎች አመራር አባላት በመሳተፍ…

Read More

ሀገራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ ጉዳዮች ላይ የመፍትሔ ሀሳብ በማፍለቅ የሕዝቦችን አብሮነትና ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ

በሸካ ዞን 19ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን “ሀገራዊ መግባባት ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል ተከብሯል። “ሀገራዊ መግባባት ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት”በሚል መሪ ቃል በዞኑ ባሉ ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች በተለያዩ ኩነቶች ሲከበር ቆይቶ ዞናዊ ማጠቃለያው በቴፒ ከተማ ተካሂዷል። የሸካ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ዮሀንስ ካሳሁን እንደገለፁት የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በሀገር አቀፍ…

Read More

የብልጽግና ፓርቲ የፎቶ አውደ ርዕይ በሳይንስ ሙዝዬም ተከፈተ

የብልጽግና ፓርቲ አምስተኛ ዓመት የምስረታ በዓልን አስመልክቶ የፎቶ አውደ ርዕይ በሳይንስ ሙዝዬም ተከፍቷል፡፡ በመድረኩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ተመስገን ጥሩነህ፣ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ፣ የፌደሬሽን ምክርቤት አፈጉባዔ አገኘው ተሻገር እና ሌሎች የፓርቲውና የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡ እስከ ነገ ለዕይታ…

Read More

የ19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል የዳውሮ ዞን ማጠቃለያ መርሃ-ግብር በተለያዩ ዝግጅቶች ተከበረ

“ሀገራዊ መግባባት፤ ለህብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል የሚከበረው 19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል የዳውሮ ዞን ማጠቃለያ መርሃ-ግብር በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል። በበዓሉ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዳዉሮ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ዳዊት ሚኖታ፤ 19ኛው የኢትዮጵያ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዞኑ በተለያዩ ኩነቶች ከቀበሌ እስከ ትምህርት ቤቶች ደረጃ ሲከበር መቆየቱን ገልጸዋል።…

Read More

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ለትምህርት ጥራት አጋዥ የሆኑ ኮምፒውተሮችን ለዞኖች አሰራጨ

የደቡብ ምዕራብ አትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ ከካማራ ኢዱኬሽን ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ግዢ የተፈጸመባቸው ለትምህርት ጥራት አጋዥ የሆኑ ኮምፒውተሮችን ለዞኖች አሰራጭቷል ። የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምትክልና የስርአት ትምህርት ዘርፍ ሃላፊ አቶ አባተ ኡቃ እንደገለጹት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የኮምፒውተር ግዢው እንደተፈጸ ገልጸዋል። የኮምፒውተር ስርጭቱ የትምህርትን ስራ ከቴክኖሎጂ ጋር ለማገናኘትና ውጤታማ…

Read More