በቦንጋ ከተማ የወባ ወረርሽኝ የሚራባባቸውን አካባቢዎች የማጽዳትና ፍሳሾችን የማስወገድ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
የወባ ወረርሽኝ ስርጭት ለመግታት “ረቡዕን ለወባ” የሚል የጽዳት ዘመቻ ዛሬ በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል። እንደ ሀገር የወባ ወረርሽኝ በህብረተሰቡ ጤና ላይ የሚያስከትለውን ጉዳት ከግንዛቤ በማስገባት በዞኑ በተለያዩ አካባቢዎች የግልና የአካባቢ ጽዳት ዘመቻ ሲደረግ መቆየቱ ይታወቃል። ይህንን አምራቹን ኃይል እየጎዳ ያለውን የወባ ወረርሽኝ ለመከላከል እንደ ካፋ ዞንም ይሁን እንደቦንጋ ከተማ የተለያዩ የጽዳትና የማፋሰስ ሥራዎች ዛሬም እየተሰሩ ይገኛሉ።…
