Trendings

Getenesh Gebeyehu

ሞትን አምልጠው፤ ምርጫን አሸንፈው ኋይትሃውስ የገቡት ፕሬዚዳንት

ዶናልድ ትራምፕ ሦስት ጊዜ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ለመሆን ሙከራ ከማድረጋቸው በፊት በአሜሪካ ታዋቂ እና አነጋጋሪ ቢሊየነር እንዲሁም በቴሌቭዥን መስኮት የማይጠፉ ዝነኛና አለፍ ሲሉም አስገራሚ ፖለቲከኛ ስለመሆናቸው ይነገራል። (Make American great again) አሜሪካንን መልሶ ታላቅ ማድረግ በሚለው መለያቸው በአውሮፓውያኑ 2016 ምርጫ ብቅ ያሉት ትራምፕ የሪፐብሊካን ፓርቲ ዕጩ ሆነው ነበረ ከዲሞክራቷ ሂላሪ ክሊንተን ጋር የተፎካከሩት። በ2016 የምርጫ ቅስቀሳቸው…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ ታዋቂ ሰዎች አጀንዳ የማሰባሰብ ውይይት ዛሬም ቀጥሏል።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ታዋቂ ሰዎች ጋር አጀንዳ የማሰባሰብ ውይይት ተጀምሯል። ኮሚሽነር ዘገየ አስፋው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ የተሰባሰቡ ታዋቂ ሰዎች በአካባቢያቸው ህዝብን በማስተባበር ብዙ መስራት የቻሉ መሆናቸውን ተናግረዋል ። በሚኖረው የአጀንዳ ማሰባሰብ ውይይት ላይ የምታፈልቁት ሀሳብ በግብታዊ ሳይሆን መሠረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ መሆን እንዳለበት ኮሚሽነር ዘገዬ አሳስበዋል ።…

Read More

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚያከናዉናቸው ተግባራት ውጤታማ እንዲሆን የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ የድጋፍና ክትትል ስራዎችን እንደሚያጠናክር አስታወቀ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ፋይናንስ ቢሮ እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የ3ኛ ዙር የጋራ ምክክር መድረክ በሚዛን ከተማ አካሂዷል ። በምክክር መድረኩ በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅች በኩል የተከናወኑ የስራ አፈጻጸም ረፖርት ቀርበው ከተሳታፊዎች ሀሳቢና አስተያየት ተነስተው ውይይት ተደርጎበታል። በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ መቱ አኩ እንደተናገሩት ድርጅቶች በክልሉ በተለያዩ ዘርፎች…

Read More

የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደቱ ግለፀኝነትና አሳታፊ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮች ገለፁ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል እየተከናወነ ያለውን 3ኛ ቀኑን የያዘውን የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ አስመልክቶ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በቦንጋ ከተማ መግለጫ ሰጥቷል። በመግለጫው ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሉጌታ አጎ የእስካሁን ያለውን የምክክሩን ሂደት ከሁሉም ወረዳዎች የተመረጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ወኪሎች ግልጽና አሳታፊ በሆነ መልኩ አጀንዳቸውን አደራጅተው ያጠናቀቁበት የምክክር መድረክ መሆኑን ገልፀዋል። በክልሉ የህብረተሰብ ወኪሎች…

Read More

ሀገራዊ ሪፎርም ከተጀመረ በኋላ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ የመጠባበቂያ ክምችት በእጥፍ አድጓል

ሀገራዊ ሪፎርም ከተጀመረ በኋላ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ የመጠባበቂያ ክምችት በእጥፍ ማደጉን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምሕረቱ አስታወቁ፡፡ አዲሱ የብሔራዊ ባንክ ማሻሻያ አዋጅ ከዚህ ቀደም ለረዥም ዓመታት ሲሠራበት የቆየውንና ለዋጋ ንረት ዋና መነሻ ነበር ሲባል በቆየው አሠራር ላይ ጠበቅ ያለ የማሻሻያ ድንጋጌ ይዞ መቅረቡን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምሕረቱ ከሴንትራል ባንኪንግ መጽሔት ጋር ባደረጉት…

Read More

የ’World Without Hunger’ ጉባኤ ተሳታፊዎችን እንኳን ወደ አፍሪካ የዲፕሎማሲ መዲና በሰለም መጣችሁ እላለሁ።

አለምአቀፍ መሪዎችን፣ ባለሞያዎችን እና የጉዳዩ ተቆርቋሪዎችን በአንድ ላይ በማምጣት እንዲወያዩ በማድረግ የጋራ ጥረቶቻችን ረሃብን በማጥፋት ለሁሉም የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ርብርብ ፍሬ እንዲያፈራ እንደሚያስችሉ ተስፋ አለኝ። በኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ዓመታት በግብርና ሽግግር እና ምርታማነት ላይ በማተኮር የሠራነው ሥራ የታረሰ መሬታችን እጥፍ በማድረስ ከፍ ያለ እሴት ባላቸው የኢንደስትሪ አዝርዕት ምርት ላይ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች አስገኝቷል። በሚቀጥሉት ቀናት…

Read More

የክልሉ ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በተጨባጭ እንዲረጋገጥ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በመቀራረብ እየተሰራ ነው፦አቶ ነጋ አበራ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግሥት ፋይናንስ ቢሮ እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የ3ኛ ዙር የጋራ ምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ነው። በምክክር መድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ መንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ነጋ አበራ የክልሉ መንግስት ፈጣንና ቀልጣፋ የልማት ስራዎችን ለህዝቡ ተደራሽ ለማድረግ በርካታ የአሰራር ስርዓቶችን በመዘርጋት እየሰራ እንደሆነ ጠቁመዋል። በዚህም የክልሉ ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት…

Read More

ሀገራዊ ምክክሩ በሀገራችን እስከአሁን የነበሩ ችግሮች በንግግርና በምክክር ለመፍታትእጅግ ጠቃሚ ነው፦ አስተያየት ሰጪ መምህራንና የመንግሥት ሠራተኞች

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትናንት ጥቅምት 24/2017 ዓ.ም በጀመረው አጀንዳ ማሰባሰቢያና ተወካይ መረጣ መድረክ እየተሳተፉ የሚገኙ በክልሉ ከሁሉም ዞኖች የተወጣጡ የማህበረሰብ ክፍሎች ከትላንት ከሰዓት ጀምረው አጀንዳዎቻቸውን በቡድን ሲያደራጁ ቆይተዋል፡፡ በመድረኩ እየተሳተፉ የሚገኙ መምህራንና መንግሥት ሠራተኞች የምክክር ሂደቱ የሀሳብ የበላይነትንና ነፃነትን ለማረጋገጥ እጅግ ጠቃሚ መሆኑን ተናግረዋል ፡፡ ከተሳተፉት መምህራን መካከልም መ/ር ንጉሴ ዓለሙ ከካፋ ዞን…

Read More

የወረዳ የማህበረሰብ ወኪሎች በአጀንዳዎቻቸው ላይ እየተወያዩ ነው፡፡

#ደቡብ_ምዕራብ_ኢትዮጵያ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የምክክር መድረክ እየተሳተፉ የሚገኙ የማህበረሰብ ወኪሎች ከትላንት ጥቅምት 24/2017 ዓ.ም ከሰዓት ጀምረው ከወከሉት ማህበረሰብ ይዘዋቸው የመጡ አጀንዳዎችን በውይይት በማደራጀት ላይ ናቸው፡፡ በዚህ የምክክር መድረክ ከ57 የክልሉ ወረዳዎች የተወጣጡ 1003 የሚሆኑ የዘጠኝ የማህበረሰብ ክፍል ወኪሎች በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡ እነዚህ የወረዳ የማህረሰብ ክፍል ወኪሎች ምክክራቸውን እስከ ነገ ማክሰኞ ጥቅምት 26/2017 ዓ.ም ድረስ…

Read More

ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ ለደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ የቦርድ አመራር ምደባ ሰጡ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት በወጣ አዋጅ የተቋቋመዉ የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ምደባ ሰጥተዋል። በዚህ መሠረት 1.አቶ ጸጋዬ ማሞ …..ሰብሳቢ 2.አቶ ነጋ አበራ…….ም/ሰብሳቢ 3.አቶ ፋጂዮ ሳፒ…… አባል 4.አቶ የሺዋስ ዓለሙ….አባል 5.አቶ አንድነት አሸናፊ….አባል 6.አቶ ንጉሴ ወ/ጊዮርጊስ…….አባል የሚዲያ ኔትወርክ የቦርድ አመራር ሆነዉ ተመድበዋል።

Read More