የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚያከናውነው የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ ነገ ይጀመራል
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከነገ ጀምሮ የሚካሄደውን የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረክ በተመለከተ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዘገየ አስፋው እና ኮሚሽነር ሙሉጌታ አጎ በጋራ በቦንጋ ከተማ ተገኝተው ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ኮሚሽነሮቹ በመግለጫቸው በምክክር ሂደቱ ቁልፍ ከሆኑ ተግባራት መካከል አጀንዳዎች አካታችና አሳታፊ በሆነ ሂደት የማሰባሰብ እንዲሁም በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ የሚሳተፉ ተወካዮች የማስመረጥ ተግባር በመሆኑ ለዚህም ኮሚሽኑ…
