Trendings

Getenesh Gebeyehu

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና መሰጠት ጀመረ

የ2016 ዓ.ም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና መሰጠት ጀምሯል። በዛሬው ዕለት የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲዎች ፈተናቸውን እየወሰዱ መሆኑ ታውቋል፡፡ ፈተናውን በይፋ ያስጀመሩት የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)÷ ዛሬ የሚሰጠው ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ የበይነ መረብና የወረቀት ፈተና በድብልቅ ነው ብለዋል። በመላ ሀገሪቱ የተጀመረው የበይነ መረብና የወረቀት ፈተና እንደ ሀገር…

Read More

በጎነትን ለማስረጽ እና የአብሮነት እሴቶችን ለማጎልበት የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ሚና ከፍተኛ ነው ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶች ህፃናት እና ወጣቶች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ገነት መኩሪያ ገለፁ።

የ2016 የወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልገሎት ተሳታፊዎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን የተለያዩ በጎ ተግባራትን አከናውነዋል ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ሴቶች ህፃናት እና ወጣቶች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ገነት መኩሪያ እንደገለፁት ወሰን ተሻጋሪ የክረምት ወራት በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ሠላምን አስተማማኝና ዘላቂ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን ውጤታማ ለማድረግ ሚናቸው የጎላ ነው…

Read More

በጥናትና ምርምር የተደገፉ ውሳኔዎችና የአሠራር ሥርዓቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ – አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ

በጥናትና ምርምር የተደገፉ ውሳኔዎችና የአሠራር ሥርዓቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አራተኛውን ዓመታዊ የፓርላማ ጥናትና ምርምር ኮንፍረንስ በአዲስ አበባ እያካሄደ ነው። በመርኃ-ግብሩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎን ጨምሮ ምክትል አፈ-ጉባዔ ሎሚ በዶ፣ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና የምክር ቤት አባላት፣ ሚኒስትሮች፣ የክልል አፈ-ጉባዔዎች፣ ለምክር ቤቱ ተጠሪ…

Read More

መገናኛ ብዙሃን ለብሔራዊ ጥቅም መከበርና ለዜጎች አብሮነት መጎልበት ያለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጡ ይገባል – አቶ መሀመድ እድሪስ

መገናኛ ብዙሃን ለብሔራዊ ጥቅም መከበርና ለዜጎች አብሮነት መጎልበት ያለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሀመድ እድሪስ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሀመድ እድሪስ ለኢዜአ እንዳሉት፤ መገናኛ ብዙሃን ለብሔራዊ ጥቅም መከበርና ለህዝብ አብሮነት መጠናከር ከፍተኛ ሚና አላቸው፡፡ ይህንን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት ከመገናኛ ብዙሃን የሚጠበቅ መሆኑን አንስተው፤ በተቃራኒው አንዳንድ መገናኛ…

Read More

በዳውሮ ዞን፣ ዛባ ጋዞ ወረዳ በዩኒሴፍና በመንግሥት ትብብር የተገነባው የዳቼ ደነባ ንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀከት ተመረቀ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን፣ ዛባ ጋዞ ወረዳ ዳቼ ደነባ ቀበሌ በመንግሥትና በዩኒሴፍ የገንዘብ ድጋፍ የተገነባው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የክልሉ የውሃ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር በየነ በላቸው በተገኙበት ተመርቋል። በወንድማገኝ አየለ ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ የተገነባው ይኸው የውሃ ፕሮጀክት 18 ኪሎሜትር የመስመር ጥገና፣ 75 ሺህ ሊተር የውሃ ማጠራቀሚያ እና 9 የውሃ ቦኖ እንዲሁም የከብት…

Read More

እንደ ንብ ታታሪዋ እንስት ››

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት በንብ ሀብት እምቅ አቅም እንዳለው ይታወቃል፡፡ የማርና ሰም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በክልሉ ከባለፉት ዓመታት ጀምሮ በንብ ሀብት የተቀረጹ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ተግባራዊ መሆን ጀምሯል፡፡ የተለያዩ የእንስሳት ልማት የቴክኖሎጂ/ጥንቅሮች ወይም ፓኬጆች ተዘጋጅተው በየአካባቢው እንደ አመችነታቸው እዲተገበሩ የማድረግ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል፡፡ በቀበሌ ደረጃ የእንስሳት ሀብት ዘርፍ የልማት ጣቢያ ሠራተኞችን በማሰማራት ለተጠቃሚ አናቢዎች…

Read More

የመጀመሪያው የኢትዮጵያ-ደቡብ ሱዳን የጋራ ድንበር አስተዳዳሪዎች የምክክር መድረክ ተጀመረ

የመጀመሪያው የኢትዮጵያ-ደቡብ ሱዳን የጋራ ድንበር አስተዳዳሪዎች የምክክር መድረክ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ውስጥ ዛሬ ተጀምሯል። ለሁለት ቀናት የሚቆየው መድረኩ በልማት ትብብር፣ በጋራ የመሠረተ ልማት ዝርጋታ እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ማሳደግ ላይ ሀሳብ ለመለዋወጥ ያለመ ነው። በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ፍስሃ ሻውል፣ በመድረኩ ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፣ ለድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች የጋራ መፍትሄ…

Read More

ስራ ፈጣሪ ዜጋን ለማፍራት ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ትምህርት ኮሌጅ ያለው ሚና የጎላ መሆኑ ተገለፀ

የቃራዎ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰለጠናቸውን 89 ሰልጣኞች በዛሬው ዕለት አስመርቋል፡፡ በዳውሮ ዞን ከሚገኙ አምስት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት መካከል የቃራዎ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ አንዱ ሲሆን ኮሌጁ በ2013 ዓ.ም ወደ ስራ መግባቱን ኮሌጁ ዲን አዲሱ ዘካሪያስ ገልፀዋል። በዚህም በሰባት ትምህርት ዘርፎች በርካታ ሰልጣኞች እያሰለጠነ ሲሆን በዛሬው ዕለት በአይስቲና (ICT) እና በኮንስትራክሽን ሙያ ዘርፍ በመደበኛና በማታ…

Read More

ተመራቂ ተማሪዎች በተማሩት መስክ ለሀገራቸው እድገትና ብልፅግና የበኩላቸውን መወጣት አለባቸው:- አቶ ፀጋዬ ማሞ

የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመርቋል። በምረቃ ስነ-ስነ ስርዓቱ ላይ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦቸ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፀጋዬ ማሞ ተመራቂ ተማሪዎችን እንኳን ደስ አላችሁ ብለው ምሩቃን የተሻለ ባገኙት እውቀት ለሀገር እድገትና ብልፅግና የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል። ዩኒቨርሲቲው በሁሉም መስክ በመሻሻል ላይ ነው ያለው ያሉት አቶ ፀጋዬ ማሞ…

Read More

ቋሚ ኮሚቴው የ2016 በጀት ዓመት የአስፈጻሚ አካላትን ማጠቃለያ ሪፖርት እየገመገመ ይገኛል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የአምስቱም ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ የ2016 በጀት ዓመት የአስፈጻሚ አካላትን ማጠቃለያ ሪፖርት በታርጫ ከተማ እየገመገመ ይገኛል። የሪፖርት ግምገማ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፌጉባኤ ወንድሙ ኩርታ በክልሉ የማሀበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ ዕድገት ፋይዳ ያላቸውን ተግባራት አፈጻጸም ተከታትለው መገምገምና ማረም የምክር ቤቱ ተልዕኮ መሆኑን በመግለጽ ከዚህም አኳያ የክልሉ ምክር…

Read More