Trendings

Getenesh Gebeyehu

ሪፖርታዥ

በክልሉ የግብርና ልማት ግቦች እንዲሳኩ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ የሚገኝ ፕሮግራም ፦ በክልሉ ግብርና ቢሮ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነት ለማስጠበቅ ብሎም የዜጎችን የስነ ምግብ ስርዓትን ለማሻሻል እና በዘርፉ የስራ ዕድል ለመፍጠር ዘርፌ ብዙ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ፤ በዚህም በዘርፉ አበረታች ውጤትም እየተመዘገበ ይገኛል። የክልሉ ግብርና ቢሮ የክልሉን የመልማት አቅም በመለየት ቴክኖሎጂዎችን በማስተዋወቅና በማስረጽ፣ የኤክስቴንሽን ስርዓቱን…

Read More

ሰላምን በማጽናት ልማትን ለማረጋገጥ መንግስትና ህዝብ እጅ ለእጅ ተያይዘው መስራት እንዳለባቸው ተገለጸ።

በደብረ ብርሃን ከተማ” የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች” በሚል መሪ መልዕክት ሕዝባዊ ውይይት እየተካሄደ ነው። በውይይቱ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና ግብርና ቢሮ ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ የተከበሩ ማስረሻ በላቸው፣ና የሸገር ከተማ ከንቲባና የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) ጨምሮ የከተማው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ‎የደብረ ብርሃን ከተማ…

Read More

በመደመር መንግሥት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ የካፋ ዞን እና የቦንጋ ከተማ እያንሰራራ ነው – ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር)

“የጉባ ብስራቶች፣የመደመር ትሩፋቶች” በሚል መሪ ቃል በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ ካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ የተዘጋጀው የህዝብ ዉይይት መድረክ ተጠናቋል። በመድረኩ ማጠቃለያ ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት በኢፌዲሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትርና የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፥ በመደመር መንግሥት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሆነ የቦንጋ ከተማ እያንሰራራ…

Read More

በአከባቢው በብዝሀ ዘርፍ ያለውን እምቅ አቅም ወደ ብልፅግና ለመቀየር የሥራ ባህልን በመቀየር መሥራት ያስፈልጋል ፦ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ

”የጉባ ብስራቶች፣የመደመር መንግስት ትሩፋቶች” በሚል መሪ ቃል በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሚዛን አማን ከተማ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩ የብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት የሕዝብና ዓለም-አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በአከባቢው በብዝሀ ዘርፍ ያለውን እምቅ አቅም ወደ ብልፅግና ለመቀየር የሥራ ባህልን በመቀየር ጠንክሮ መሥራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለተረጂነት የሚመች…

Read More

ስር የሰደዱ ችግሮችን አሸንፈን ወደ እውነተኛ ብልጽግና እየገሰገስን እንገኛለን፦ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር )

“የጉባ ብስራቶች፤ የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች” በሚል መሪ ሃሳብ በሐረር ከተማ ሕዝባዊ የውይይት መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩ መልእክት ያስተላለፉት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድርና የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የመደመር መንግስትና ፓርቲያችን ስር የሰደዱ ችግረኞችን በመቅረፍ፣ የገጠሙንን ፈተናዎች ወደ እድል በመቀየር ወደ ስኬት ጎዳና እየተንደረደርን እንገኛለን ብለዋል ። ፓርቲያችን ፈተናዎችን…

Read More

በግብርና ዘርፍ ለወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

በግብርናው ዘርፍ በተሰጠው ትኩረት ለወጣቶች የስራ ዕድል በመፍጠር ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የጣሎ ወረዳ ግብርና ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ጽህፈት ቤት ገልጿል። የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ አፋወርቅ አደመ በአካባቢውን ያለውን ፀጋ በመጠቀም በወረዳው በዓመት ከ2300 ሄክታር በላይ አትክልትና ፍራፍሬ ማልማት 320ሺ ኩንታል በላይ ምርት ወደ ገበያ ማቅረብ መቻሉን ተናግረዋል። ከዚህም በመነሳት ከአረንጓዴ አሻራ ኢንሼቲቭ…

Read More

vbdfg

የኢፌዴሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የድጋፍና ክትትል ቡድን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የሥራ እንቅስቃሴ ዙሪያ ከቢሮ ኃላፊዎችና ማናጅመንት አካላት ጋር ተወያይተዋል። የድጋፍና ክትትል ቡድን ዓላማዉ፤ ክልላዊ የኮሙኒኬሽን እና የህዝብ ግንኙነት ሥራዎች ያለበት ደረጃ በመገምገም ጥንካሬዎችን ማስቀጠል እንዲሁም ክፍተቶችን በመሙላት የቀጣይ ሥራዎች የተቀላጠፈ እንዲሆን ለማስችል ነዉ። የኢፌዲሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ድጋፍ ቡድን፣…

Read More

ከመማር ማስተማር ተግባር በተጓዳኝ በግብርና ሥራ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ መኾኑን የኢሞታ ትምህርት ቤት አስታወቀ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ በኮንታ ዞን የሚገኘው የኢሞታ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በግብርና ሥራ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ መኾኑን መመልከት ተችሏል። የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ያዕቆብ ከተለ፥ ትምህርት ቤቱ ሙሉ በሙሉ በዞኑ ልማት ማኅበር ስር እንደሚተዳደር በመግለጽ፣ ከመማር ማስተማር ተግባር ጎን ለጎን በሚያከናውነው የግብርና ልማት ሥራ ውጤታማ ነው ብለዋል። በመደበኛ የመማር ማስተማር ተግባር፣ ትምህርት…

Read More

dc

በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ አስተዳደር ቅዱስ ዮሰፍ ካቶሊክ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው ክትባቱን ያስጀመሩት የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ የነገ ሀገር ተረካቢ የሆኑ ህጻናትን ጤና ለመንከባከብ መንግስት እንደ ሀገር መጠነ ሰፊ ሥራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በዚሁ ሂደት ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውንና የአገልግሎት ተደራሽነቱንም ከፍ ለማድረግ መቻሉን ዋና አስተዳዳሪው አመላክተዋል። እንደ ዞን በእናቶችና ህጻናት…

Read More

የኢፌዲሪ ጦር ሃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ ለይፋዊ የሥራ ጉዳይ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ገቡ።

ጄኔራል አበባው ወደ ክልሉ፣ ቦንጋ ከተማ ሲደርሱ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል አድረገዋል። ጄኔራል አበባው በክልሉ በሚኖራቸው ቆይታ በሠላምና ፀጥታ ጉዳይ ከክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሀላፊዎች ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ተገልጿል። በዕድገቱ በዛብህ

Read More