በሚዛን አማን ከተማ የኮሪደር ልማት እና ፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ እየተካሄደ ነው::
የሚዛን አማን ከተማን ዕድገትና የህዝቡን ፍላጎት ባማከለ መልኩ መልሶ ለማልማት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ ነው። የኮሪደር ልማት ሥራን በከተማ አስተዳደር ደረጃ ማስጀመር እና ጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄን ማስጀመርን ዓለማ ያደረገ ግንዛቤ ማስጨበጫና ምክክር ነው እየተካሄደ ያለው። የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን ከተሞች ቀደም ሲል ደረጃውን ባልጠበቀ ፕላን የተመሠረቱ ሲሆን አሁን ላይ ያለውን…
