የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአንዳንድ ኤምባሲዎች የደቦ መግለጫዎች ተቀባይነት እንደሌላቸው አስታወቀ
ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ አንዳንድ ኤምባሲዎች በደቦ የሚያወጧቸውን መግለጫዎች ኢትዮጵያ እንደማትቀበል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ነብዩ ተድላ የሀገሪቱን አበይት የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴዎች አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአዲስ አበባ የሚገኙ አንዳንድ ኤምባሲዎች የሚያወጧቸው የጋራ መግለጫዎች ከተለመደው የዲፕሎማሲ አሰራር ያፈነገጡ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ ባለፈው ሳምንት የዓለም የፕሬስ ቀንን ምክንያት በማድረግ አንዳንድ ኤምባሲዎች…
