Trendings

በሸገር ከተማ አስተዳደር በከባድ የማታለል ወንጀል ሲፈለግ የነበረውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግኝኙነትና ኮሚንኬሽን ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ በሸገር ከተማ አስተዳደር በመልካ ኖኖ ክፍለ ከተማ በተለያዬ አራት ሀሰተኛ ስሞችን በመጠቀም በ15 ግለሰቦች ላይ በከባድ የማታለል ወንጀሎች በመፈፀም ክስ ተመስርቶበት በፖሊስ ሲፈለግ መቆየቱን ፖሊስ ኮሚሽኑ ገልጿል። የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ተጠርጣሪውን በተገኘበት እንዲያዝ ከፍርድ ቤት መያዣ ጋር በመላካቸው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ…

Read More

የሥራ አጥ ቁጥርን ለመቀነስ የሚከናወኑ ሥራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ ድጋፍና ክትትሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል – የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር::

በክልሎችና በከተሞች የሥራ አጥ ቁጥርን ለመቀነስ የሚከናወኑ ተግባራት ስኬታማ እንዲሆኑ የሚደረገው ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ዳንኤል ተሬሳ ገለጹ። በአቶ ዳንኤል ተሬሳ የተመራ የሚኒስቴሩ የባለሙያዎች ቡድን በምስራቅ ኢትዮጵያ በሚገኙ ክልሎች በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ የተሰሩ ሥራዎችን ተዘዋውሮ እየተመለከተ ይገኛል። ቡድኑ በዛሬው ዕለት ከድሬዳዋ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊና አመራሮች ጋር…

Read More

በፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር ኢትዮጵያ የላቀ ውጤት እንድታስመዘግብ ዝግጅት እየተደረገ ነው::

በፈረንሳይ ፓሪስ በሚካሄደው ኦሎምፒክ ውድድር ኢትዮጵያ የላቀ ውጤት እንድታስመዘግብ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ከአማራ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር በደሴ ከተማ የኦሎምፒክ ችቦ ማብራትና ቅብብሎሽ መርሃ-ግብር አካሂዷል፡፡ እንደኮሚቴው አገላለጽ የፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ ውድድር በመጪው ሐምሌ ወር እንደሚካሄድም ታወቋል። በውድድሩ ኢትዮጵያ የተሻለ ውጤት እንድታስመዘገብ ከወዲሁ የቅደመ ዝግጅት ስራ እየተከናወነ…

Read More

ኢትዮ ቴሌኮም “ቴሌ ብር ኢንጌጅ” የተሰኘ አዲስ አገልግሎት ይፋ አደረገ::

ተቋሙ ለአገልግሎት ያበቃው አዲሱ መተግበሪያ በቴሌብር ሱፐር አፕ ውስጥ የተካተተ ሲሆን በዋናነት ግብይት፣ ማህበራዊ ግንኙነትና መረጃ ልውውጥን በአንድ መተግበሪያ የያዘ ነው፡፡ አገልግሎቱን በይፋ ያስጀመሩት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ት ፍሬህይወት ታምሩ አዳዲሶቹ አገልግሎቶች የዲጂታል ህይወትን ከማቅለል ባለፈ እንደሀገር የተያዘውን የዲጂታል ገንዘብ ልውውጥ አንድ እርምጃ ወደፊት ያራምዳል ብለዋል፡፡ “ቴሌ ብር ኢንጌጅ” ደንበኞች እርስ በእርስ ወይም…

Read More

በሚቀጥሉት 10 ቀናት ዝናብ ሰጭ ገጽታዎች በበልግ ዝናብ ተጠቃሚ አካባቢዎች ላይ ተጠናክረው ይቀጥላሉ::

በመጪዎቹ 10 ቀናት ዝናብ ሰጭ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በአብዛኛዎቹ የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ እየተጠናከሩ እንደሚቀፅሉ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ፡፡ በዚህ መሰረትም በደቡብ ምዕራብ፣ በደቡብ፤ በመካከለኛው፣ በምስራቅ፣ እንዲሁም በስምጥ ሸለቆ አካባቢዎች የተሻለ ጥንካሬ እንደሚኖራቸው ተጠቅሷል፡፡ በመሆኑም በበልግ አብቃይ አካባቢዎች በርካታ ቦታዎቻቸውን የሚሸፍን ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ነው የተገለጸው፡፡ ደቡብ ምዕራብ፣ ደቡብና በመካከለኛው…

Read More

ኢትዮጵያ እና ኔዘርላንድ በንግድ እና ኢንቨስትመንት ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለፁ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ዛሬ ከኔዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀንኬ ብርነስ ሰዋት ጋር ውይይት አድርገዋል። ውይይታቸው የሁለቱ አገራትን ግንኙነት እና ትብብር በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። አምባሳደር ታዬ በወቅቱ እንዳሉት የኔዘርላንድ መንግስት ከኢትዮጵያ ጋር በልማት ትብብር፣ በኢንቨስትመንት እና በሰብአዊ ዕርዳታ ድጋፍ መስክ ያለውን ትብብር አድንቀዋል። ተጨማሪ ትብብሮችን ለማጎልበት በሚያስችሉ የኢኮኖሚ መስኮች አብሮ መስራት…

Read More

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የሚያግዛትን 5ኛ ዙር ድርድር በግንቦት ወር ታካሂዳለች – አቶ ገብረመስቀል ጫላ

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የሚያግዛትን 5ኛ ዙር ድርድር በግንቦት ወር እንደምታካሂድ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ገብረ መስቀል ጫላ ገለፁ። አቶ ገብረ-መስቀል ጫላ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ከ20 ዓመታት በፊት የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን እንቅስቃሴ ጀምራለች። ይሁንና በኮቪድ 19 ወረርሽኝና በሌሎች ምክንያቶች ድርድሩ ተቋርጦ እንደነበር የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የጀመረችውን…

Read More

በኢትዮጵያ ለሚገኙ ስደተኞች ዲጂታል መታወቂያ ተደራሽ የማድረጉን ስራ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው

በኢትዮጵያ ለሚገኙ ስደተኞች ዲጂታል መታወቂያ ተደራሽ የማድረጉን ስራ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት አስታወቀ። የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ከብሔራዊ መታወቂያ ፕሮጀክትና ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ለሚገኙ ስደተኞች ዲጂታል መታወቂያ መስጠት መጀመሩን ከአንድ ወር በፊት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። ዲጂታል መታወቂያው በኢትዮጵያ ለሚገኙ ስደተኞች ማህበራዊ አገልግሎቶችን በተደራጀ…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በወጣትነት ዘመናቸው ሰላም አስከባሪ በመሆን ጭምር ሩዋንዳን ከችግር ለመታደግ አግዘዋል፡ – ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሚ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በወጣትነት ዘመናቸው ሰላም አስከባሪ በመሆን ጭምር ሩዋንዳን ከችግር ለመታደግ አግዘዋል ሲሉ የሩዋንዳው ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሚ ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሩዋንዳውያን የ”ኪዊቡካ 30″ ዓመት መታሰቢያ መርሐ ግብር ላይ ታድመዋል፡፡ መርሃ ግብሩ በሩዋንዳ የተፈጸመውን የዘር ጭፍጨፋ 30ኛ ዓመት የሚያስብ ነው፡፡ በመርሃ ግበሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የሩዋንዳው ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሚ ሩዋንዳን በወቅቱ ከገጠማት…

Read More

በፓሪስ የኢትዮጵያን ቱሪዝም የማስተዋወቅ መርሃ ግብር ተካሄደ::

በፓሪስ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በቱሪዝም መስክ የተሰማሩ ባለሙያዎችን እና ተቋማትን ያሳተፈ የቱሪዝም ማስተዋወቅ ኩነት አካሂዷል። በፈረንሳይ የኢትዮጵያ አምባሳደር ማህሌት ሃይሉ በመርኃ-ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ የበርካታ ሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ መስህብ ባለቤት መሆኗን ጠቅሰው ሃብቱን ለማልማት ከመቼውም ጊዜ የበለጠ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የዓለም ቱሪዝም ድርጅት ትንበያን ዋቢ በማድረግም ኢትዮጵያ ከዓለም ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻዎች አንዷ…

Read More