የወረዳውን መሠረታዊ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች ለመፍታት የህዝብን አቅም መጠቀም ይገባል። ሀብታሙ ካፍትን
የጊዲ ቤንች ወረዳ ልማት የሀብት አሰባሰብ ስራዎች ይፋዊ አጀማመር ዙሪያ በቤንች ሸኮ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን የተመራ የወረዳ አስተዳዳሪችና የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች የወረዳውን የልማት ሥራዎች ጉብኝት አካሂዷል። የጊዲ ቤንች ወረዳ በቤንች ሸኮ ዞን በለውጡ መንግስት ከተደራጁ ወረዳዎች ውስጥ አንዷ ናት። ወረዳዋ 36 ሺህ ሄክታር ስፋት መሬት ያላት ሲሆን ወደ 100 ሺህ የሚጠጋ ህዝብ ያላት…
