Trendings

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በዩኒሴፍ ፕሮግራም ገንዘብ ድጋፍ በተሰሩ ስራዎች ከፍተኛ አፈጻጸም ተመዝግቧል፦ወ/ሮ ወሰነች ቶማስ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ የ2016 በጀት ዓመት የዩኒሰፍ ፕሮግራም አፈጻጸም በቦንጋ ከተማ ገምግሟል። በክልሉ ዩኒሴፍ ፕሮግራም ገንዘብ ድጋፍ በስምንት ቢሮዎች እና በ17 ወረዳዎች የተለያዩ ፕሮግራሞች እየተከናወነ ይገኛል። የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ወሰነች ቶማስ በወቅቱ እንደገለጹት በ2016 በጀት ዓመት በክልሉ በዩኒሴፍ ፕሮግራም ገንዘብ ድጋፍ በስምንት ቢሮዎችና በ17 ወረዳዎች…

Read More

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በአገራችን የረጅም ጊዜ ታሪክ ያለውና ከህዝባችን ታሪክ፣ እሴቶች እና ማህበራዊ መስተጋብሮች ውስጥ የሚንጸባረቅና የተቆራኘ አገልግሎት እንደሆነ ታሪክ ይነግረናል፡፡

በ1996 ዓ.ም ተቀርፆ ተግባራዊ የተደረገው የወጣቶች ብሄራዊ ፖሊሲ ክፍል አምስት ላይ ወጣቶች በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ የአካባቢ ጥበቃና ማህበራዊ አገልግሎት እንቅስቃሴ ውስጥ በንቃት ተሳትፈው እራሳቸውንና ማህበረሰባቸውን ሊጠቅሙ የሚችሉባቸውን ሁኔታዎች ማመቻቸት እንደሚገባ በግልፅ ተቀምጧል፡፡ ይህንንም መሰረት በማድረግ በ2002 ዓ.ም የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን በተቀናጀ አግባብ ለመምራትና ብዛት ያላቸው ወጣቶች በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ እንዲሰማሩ ለማድረግ የሚያስችል…

Read More

በክልሉ የሚገኙ ፀጋዎችን ከቴክኖሎጂ ጋር በማስተሳሰርና በማስደገፍ ወደ ውጤት ለመቀየር እንደሚሰራ ተገለጸ።

የኢፌዴሪ ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ኢኖቬሽን እና ኢንዱስትሪ ቢሮ ባለድርሻ አካላት በሣይንስ እና ቴክኖሎጂ በአዲሱ ፖሊሲ ይዘት እና ስትራቴጂ አተገባበር ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ቦንጋ ከተማ ሰጥቷል። የክልሉ ኢኖቬሽን እና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛው ጋጊያብ በወቅቱ እንደገለጹት በሚኒስትር መስሪያ ቤቱ የተዘጋጀው ፖሊሲ እና እስትራቴጂ በክልሉ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚገኙ ጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድን በበይነ መረብ (Digital system) ለመስጠት የሚያስችል ማስጀመሪያ መርሃግብር ተካሄደ

በክልሉ ጤና ቢሮ የጤናና ጤና ነክ ተቋማት ቁጥጥር እና የባለሙያዎች ፈቃድ አሰጣጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብዱልአዚዝ ፈረጃ እንደገለጹት የጤና ባለሙያዎች ከሚሠሩበት አካባቢዎች ሳይርቁ የሙያ ፈቃድን ዲጂታላይዝ ማድረግ መቻላቸው አላስፈላጊ እንግልት የሚያስቀር ነው። ከዚህ ቀደም ባለው የአሠራር ሥርዓት በአካል ወደ ክልል ጤና ቢሮ ድረስ በመገኘት በጊዜ፣ በገንዘብና በጉልበት መባከን ላይ ሲደርስ የነበረውን እንግልት እንደሚያስቀርላቸውም ተገልጿል። ከዚህ…

Read More

ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እንዲቻል ጤናው የተጠበቀ ማኅበረሰብ መፍጠር ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ጤና ቢሮ የጤናና ጤና ነክ አገልግሎት ግብዓት ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን የዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸም በታርጫ ከተማ እየገመገመ ነው። በክልሉ ተርጫ ከተማ እየተካሄደ ባለው የዕቅድ አፈጻጸም ላይ በጤና ቢሮ የጤናና ጤና ነክ አገልግሎት ግብዓት ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን አሰፋ እንደገለጹት በ2016 በጀት ዓመት በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ጤና ለማስጠበቅ የጋራ…

Read More

የህዝቡ ልማትና ዕድገት ድምር ውጤት የሀገር ዕድገት በመሆኑ ፐብሊክ ሰርቫንቱ የአገልጋይነት ስሜት ተላብሶ ሊሰራ ይገባል፦ አቶ ሀብታሙ ካፍትን

የቤንች ሸኮ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ ከEDI ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ለዞን ሴክተር ተቋማት ለቡድን መሪዎች ለ3 ቀናት የሚቆይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ዛሬ ተጀምሯል። የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን ስልጠናውን በንግግር ሲከፍቱ እንደተናገሩት ለአንድ ሀገር ዕድገት የፐብሊክና ፋይናንስ ሴክተሮች ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል። በተለይም በእኛ ሀገር ተጨባጭ ሁኔታ ህብረተሰቡ አብዛኛውን…

Read More

የህዝብ ለህዝብ ግኑኝነት መጠናከሩ ለሀገራዊ አንድነት የላቀ አስተዋጽኦ አለው፦ አቶ ማስረሻ በላቸው

የጎንጋ ህዝቦች የልማትና የትብብር ማህበር ያዘጋጀው 6ኛው የጎንጋ ህዝቦች የልማትና ትብብር ፎረም በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በፎረሙ መክፈቻ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ የጎንጋ ህዝቦች የህዝብ ለህዝብ ግኑኝነት መጠናከር ለሀገራዊ አንድነት የላቀ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል። ግኑኝነቱን በማስፋት በህዝቦች መካከል ህብረብሔራዊ አንድነትን…

Read More

ክልሉ ከሚያመነጨው ሀብት አንፃር አጠቃላይ የገቢ መሠረቶችን በመለየት ገቢ መሰብሰብ ያስፈልጋል፦ ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ገቢዎች ቢሮ የ2017 በጀት አመት ያለፉት ሁለት ወራት የደረጀ ሐ እና ለ አፈፃፀም እንዲሁም የቀሪ ወራት የገቢ አሰባሰብ ላይ ከክልል እና ከዞን አስተባባሪ አካላት እንዲሁም ከገቢ ሴክተር ኃላፊዎች ጋር የምክክር መድረክ በቦንጋ ከተማ አካሂዷል። በምክክር መድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ክልሉ ከሚያመነጨው ሀብት አንፃር አጠቃላይ…

Read More

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ለኢሬቻ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ለኢሬቻ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በመልካም ምኞት መግለጫቸው እንደገለጹት ኢትዮጵያ ብዝሀ ማንነትና ባህሎች ተከባብሮና ተቻችሎ የሚኖሩባት የብዝሃነት ማዕከል መሆኗን በመጥቀስ ከነዚህ ውብ ባህልና ዕሴቶች አንዱ በኦሮሞ ህዝብ ዘንድ በድምቀት የሚከበረው የኢሬቻ በዓል መሆኑን ገልጸዋል። ኢሬቻ የክረምት ወራት አልፈው መጸው ሲገባ ፈጣሪ…

Read More

በክልሉ ዘላቂ ሰላምና ጸጥታን ለማዝለቅ እና ለማጽናት ከመከላከያ ሰራዊት ጋር በጋራ መስራት ወሳኝ ነው:- ዶክተር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ

ሀገራዊና ክልላዊ ሠላምና ፀጥታን በአስተማኝ ደረጃ ለማረጋገጥ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር በቅንጅት ለመስራት የሚያስችል ውይይት በቦንጋ ከተማ ተደርጓል። በውይይቱ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ እንደተናገሩት ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር በቅንጅት መስራት ሀገራዊና ክልላዊ ሰላምን ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው ብለዋል። ክልላዊ የሰላምና ጸጥታ ሁኔታ እንደተገመገመ የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ ክልሉ ከአጎራባች ሀገር ጋር የሚዋሰን በመሆኑ ከሀገር…

Read More