በበርካታ ዘርፎች የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሠራ መሆኑን የባቹማ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።
በበጀት ዓመቱ ባለፉት 5 ወራት 3 መቶ ወጣቶችን በመደበኛነት ወደ ስራ ማስገባቱን ከተማ አስተዳደሩ ጠቁሟል። ወጣቶችን በተለያዩ የስራ ዘርፎች በማሰማራት ተጠቃሚነታቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ለከተማው ዕድገት የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ እንደ ከተማ አስተዳደር ብዙ ተግባራቶች መከናወናቸውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምዕራብ ኦሞ ዞን የባቹማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አቤል ታደመ ተናግረዋል። በዚህም በበጀት ዓመቱ 5 መቶ…
