በአንድራቻ ወረዳ የጌጫ ከተማ የህዝብ መድኃኒት ቤት ተመርቆ ለአገልግሎት ብቁ ሆኗል።
የህዝብ መድኃኒት ቤቱን የክልሉ ዋና አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ መርቀዋል። በምረቃው ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ወሰን ጨመሰ መድኃኒት በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ የሚቀርብበት ነው ብለዋል። በመንግሥት ተቋማት የማይገኙ መድኃኒቶች በአማራጭነት ቀርበው ህብረተሰቡ እንዲጠቀም ያግዛልም ብለዋል። ለአገልግሎት በበቃው የህዝብ መድኃኒት ቤት የሰው ሀይል ቅጥር ለማሟላት ትኩረት ተደርጎ ይሰራል ብለዋል።…
