በፍርድ ቤቶች የዳኝነት ነፃነትን ያጠናከሩና የፍትሕ ሥርዓቱን ማዘመን ያስቻሉ ስኬታማ ተግባራት ተከናውነዋል
ባለፉት የለውጥ ዓመታት የዳኝነት ነፃነትን ያጠናከሩ፣ ግልጽነትን የፈጠሩና የፍትሕ ሥርዓቱን በቴክኖሎጂ ማዘመን ያስቻሉ ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምሕረት ገለጹ። “የዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት እመርታ፤ ለተሳካ ሀገረ መንግሥት ግንባታ!” በሚል መሪ ሀሳብ በዳኝነትና ዴሞክራሲ ተቋማት ቅንጅት ላይ የሚያተኩር ሀገራዊ መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። መድረኩ በዋናነት በሀገሪቱ የፍትህ ሥርዓት እና በዴሞክራሲ ግንባታ…
